ከትግራዩ ትህነግ ጋር አብረን እንሰራለን፤ ከጎጃሙ አማራ፤ የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድትጅት በጎጃም እዝ ጋር ግን አብረን አንሰራም፤ የገቡበት ገብተን የማያዳግም እርምጃ እንወስድባቸዋለን ....አስረስ ማረ ዳምጤ በጎጃም ምድር ተሸሽጎ ከትህነግ ጋር እየተባበረ በጎጃም ምድር በተወለዱ ፋኖዎቻችን ላይ የሚዘምትን ውስጣዊን ጠላት መንጥረን ማጽዳት አለብን ‼️‼️‼️ ምስሉ ጸሃፊውን አይወክልም። በወንድወሰን ተክሉ አስረስ ማረ ዳምጤ - የአማራ ፋኖ በጎጃም ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ የትህነጉ መሪ ዶ/ር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል በቅርቡ ከአማራ ፋኖ እና ከኤርትራው መንግስት ሻእቢያ ጋር አብረን ለመስራት እንፈልጋለን ለሚለው ገለጻው በብርሃን ፍጥነት ብቅ ብሎ «ከህወሃት ጋር አብረን እንሰራለን» በማለት ምላሽ ሰጥቷል፡፡ ይህ የአስረስ ማረ ዳምጤ ምላሽ የአንድ ግለሰብ ሳይሆን የድርጅቱ፤ ማለትም የአማራ ፋኖ በጎጃም ተብሎ የሚጠራ አንድ አደገኛ ተዋጊ ቡድን ድርጅታዊ አቌም መሆኑን መላው የአማራ ህዝብና መላው የአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች በሙሉ ሊያውቁት የሚገባ እውነታ ነው፡፡ በእርግጥ የትህነጉ ዶ/ር ደብረጺዮን ከፋኖ ጋር አብሮ ለመስራት እንፈልጋለን የሚለው አሁናዊ አባባል ዝም ብሎ ከመሬት ተነስቶ የተነገረ ሳይሆን በሁለቱ ፋሺስታዊ ቡድኖች መካከል - ማለትም በዘመነ ካሴ በሚመራው የአማራ ፋኖ በጎጃም እና በዶ/ር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል በሚመራው የትግራዩ ትህነግ መካከል በተካሄደ ምስጢራዊ ግንኙነትና ስምምነት መሰረት ዛሬ ዶ/ር ደብረጺዮን በአደባባይ የተናገሩት ሀቅ መሆኑን ማወቅና መረዳት ይገባል፡፡ ባለፈው ሀምሌ ወር ውስጥ የአማራ ፋኖ በጎጃም አመራር ነን የሚሉት አስረስ ማረ እና ማርሸት ጸሀዬ ከትግራዩ ትህነግ ከዶ/ር ደብረጺዮን ጋር ምስጢራዊ ንግግርና ድርድር ማድረጋቸውን ያጋለጥ የ
ከአሁን በሆላ ፋኖ ወደ አንድነት መምጣት አለባቸው የሚባለው አካሄድ አይሰራም:: ክህደት ከተፈፀመ በሆላ አንዱ ቡድን ከሌላው ስር ሆኖ ይቀጥላል ማለት የማይቻል ነው:: ምክኒያቱም 1ኛ:- 27 ቀን ቁጪ ብለው መክረዋል :: እያንዳንዱ አደረጃጄት ሰነድ ፅፈው አቅርበዋል:: በቀረበው ሰነድ ላይ ከፍተኛ ውይይት ተደርጎበት የሚወድቀው ወድቆ የሚፈለገው ፀድቋል::ቃለ መሀላ ፈፅመው ወደ ምርጫ ለመግባት ተስማምተዋል:: እጃቸውን አውጥተው ከመረጡ በሆላ ግን "ጨዋታ ፈረሰ ዳቦ ተቆረሰ" የሚል የህፃን ልጂ ጨዋታ ውስጥ መግባት የአማራን ህዝብም ሆነ የፋኖን ትግል መናቅ ነው:: ይህ አልበቃ ብሎ "ምርጫው ከኛ እውቅና ውጪ ነው እኛ አናውቀውም" የሚል የውሸት የህፃን ልጂ ፕሮፓጋንዳ እንዲሰራጪ አድርገዋል::ከዚህ በሆላ ይህ ቡድን የታላቁ እና የጠቢቡ የአማራ ህዝብ መሪ ነኝ ብሎ አይኑን በጨው አጥቦ ለመምጣት እንዴትስ ይደፍራል ???? የድምጽ ቅንብሩ ጸሃፊውን አይወክልም። 2ኛ:- የፋኖ ወታደራዊ ጦር ዋና አዛዢ የሆነው ሻለቃ ዝናቡ የራሳቸውን ድክመት እና ሴራ በአማራ ህዝብ ላይ ለማሸከም የአማራን ህዝብ በጂምላ ይህ "ጎጃም ጠልነት ነው" ብሎ ከወነጄለ በሆላ ይቅርታ ሳይጠየቅበት በጋራ ለአንድ አላማ እንዴትስ መስራት ይቻላል??? የአማራ ጪምብላቸውን አውልቀው እንዴትስ በመቅፅበት ወደ ጎጣቸው ተወርውረው ሊገቡ ቻሉ??? አጄንዳቸው እንዴትስ