Skip to main content

Posts

ከትግራዩ ትህነግ ጋር አብረን እንሰራለን፤ ከጎጃሙ አማራ፤ የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድትጅት በጎጃም እዝ ጋር ግን አብረን አንሰራም፤ የገቡበት ገብተን የማያዳግም እርምጃ እንወስድባቸዋለን ....አስረስ ማረ ዳምጤ ፤ በወንድወሰን ተክሉ

ከትግራዩ ትህነግ ጋር አብረን እንሰራለን፤ ከጎጃሙ አማራ፤ የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድትጅት በጎጃም እዝ ጋር ግን አብረን አንሰራም፤ የገቡበት ገብተን የማያዳግም እርምጃ እንወስድባቸዋለን ....አስረስ ማረ ዳምጤ በጎጃም ምድር ተሸሽጎ ከትህነግ ጋር እየተባበረ በጎጃም ምድር በተወለዱ ፋኖዎቻችን ላይ የሚዘምትን ውስጣዊን ጠላት መንጥረን ማጽዳት አለብን ‼️‼️‼️ ምስሉ ጸሃፊውን አይወክልም። በወንድወሰን ተክሉ አስረስ ማረ ዳምጤ - የአማራ ፋኖ በጎጃም ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ  የትህነጉ መሪ ዶ/ር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል በቅርቡ ከአማራ ፋኖ እና ከኤርትራው መንግስት ሻእቢያ ጋር አብረን ለመስራት እንፈልጋለን ለሚለው ገለጻው በብርሃን ፍጥነት ብቅ ብሎ «ከህወሃት ጋር አብረን እንሰራለን» በማለት ምላሽ ሰጥቷል፡፡ ይህ የአስረስ ማረ ዳምጤ ምላሽ የአንድ ግለሰብ ሳይሆን የድርጅቱ፤ ማለትም የአማራ ፋኖ በጎጃም ተብሎ የሚጠራ አንድ አደገኛ ተዋጊ ቡድን ድርጅታዊ አቌም መሆኑን መላው የአማራ ህዝብና መላው የአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች በሙሉ ሊያውቁት የሚገባ እውነታ ነው፡፡ በእርግጥ የትህነጉ ዶ/ር ደብረጺዮን ከፋኖ ጋር አብሮ ለመስራት እንፈልጋለን የሚለው አሁናዊ አባባል ዝም ብሎ ከመሬት ተነስቶ የተነገረ ሳይሆን በሁለቱ ፋሺስታዊ ቡድኖች መካከል - ማለትም በዘመነ ካሴ በሚመራው የአማራ ፋኖ በጎጃም እና በዶ/ር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል በሚመራው የትግራዩ ትህነግ መካከል በተካሄደ ምስጢራዊ ግንኙነትና ስምምነት  መሰረት ዛሬ ዶ/ር ደብረጺዮን በአደባባይ የተናገሩት ሀቅ መሆኑን ማወቅና መረዳት ይገባል፡፡ ባለፈው ሀምሌ ወር ውስጥ የአማራ ፋኖ በጎጃም አመራር ነን የሚሉት አስረስ ማረ እና ማርሸት ጸሀዬ ከትግራዩ ትህነግ ከዶ/ር ደብረጺዮን ጋር ምስጢራዊ ንግግርና ድርድር ማድረጋቸውን ያጋለጥ የ
Recent posts

"ከአሁን በሆላ ፋኖ ወደ አንድነት መምጣት አለባቸው የሚባለው አካሄድ አይሰራም" :: በወዳጄ/ቤተ አማራ ወሎ

ከአሁን  በሆላ  ፋኖ  ወደ  አንድነት    መምጣት  አለባቸው  የሚባለው  አካሄድ  አይሰራም::  ክህደት   ከተፈፀመ  በሆላ  አንዱ  ቡድን  ከሌላው  ስር  ሆኖ  ይቀጥላል  ማለት  የማይቻል   ነው::  ምክኒያቱም 1ኛ:- 27  ቀን  ቁጪ  ብለው   መክረዋል :: እያንዳንዱ  አደረጃጄት  ሰነድ  ፅፈው  አቅርበዋል::  በቀረበው  ሰነድ  ላይ  ከፍተኛ  ውይይት  ተደርጎበት  የሚወድቀው  ወድቆ  የሚፈለገው  ፀድቋል::ቃለ  መሀላ  ፈፅመው   ወደ  ምርጫ   ለመግባት  ተስማምተዋል:: እጃቸውን  አውጥተው   ከመረጡ  በሆላ    ግን    "ጨዋታ  ፈረሰ  ዳቦ  ተቆረሰ"   የሚል  የህፃን  ልጂ  ጨዋታ  ውስጥ  መግባት   የአማራን  ህዝብም  ሆነ  የፋኖን  ትግል  መናቅ  ነው:: ይህ  አልበቃ  ብሎ   "ምርጫው  ከኛ  እውቅና  ውጪ  ነው  እኛ  አናውቀውም"  የሚል   የውሸት    የህፃን  ልጂ  ፕሮፓጋንዳ   እንዲሰራጪ  አድርገዋል::ከዚህ  በሆላ   ይህ  ቡድን  የታላቁ  እና  የጠቢቡ   የአማራ  ህዝብ  መሪ  ነኝ    ብሎ   አይኑን   በጨው   አጥቦ  ለመምጣት  እንዴትስ  ይደፍራል ????   የድምጽ ቅንብሩ ጸሃፊውን አይወክልም።  2ኛ:- የፋኖ  ወታደራዊ  ጦር  ዋና  አዛዢ   የሆነው  ሻለቃ  ዝናቡ  የራሳቸውን   ድክመት  እና  ሴራ  በአማራ  ህዝብ  ላይ  ለማሸከም   የአማራን  ህዝብ  በጂምላ    ይህ   "ጎጃም  ጠልነት  ነው"   ብሎ  ከወነጄለ  በሆላ   ይቅርታ  ሳይጠየቅበት   በጋራ  ለአንድ  አላማ  እንዴትስ     መስራት  ይቻላል???  የአማራ   ጪምብላቸውን  አውልቀው  እንዴትስ  በመቅፅበት  ወደ  ጎጣቸው   ተወርውረው  ሊገቡ  ቻሉ???  አጄንዳቸው   እንዴትስ 

የማንቂያ ድዎል‼️ በ Alen Kassahun

የአማራ ህልውና ከመጥፋት ድኖ ዘላለማዊነቱ የሚረጋገጠው፤ ሌሎች ኢትዮጵያውያን ነገዶች ተጨፍጭፈው ከመጨፍለቅና ከመጥፋት የሚድኑት እና ኢትዮጵያ ከመፍረስና መበታተን ድና ታላቋ ትግራይና ታላቋ ኦሮሚያ በአማራ #መቃብር በኢትዮጵያውያን አፅመርስት ላይ መወለድ ቅዠት የሚሆኑት #ፋኖ አራት ኪሎን በቀጥታ በአሸናፊነት ተቆጣጥሮ  #ስርነቀል ለውጥ በኢትዮጵያ ምድር ሲያውጅ ብቻና ብቻ ነው። ፋኖ በአሸናፊነት 4ኪሎን በመቆጣጠር ስርነቀል ለውጥ ከማወጅ #በፊት የሚታሰብ ውይይት፣ ድርድር፣ የሽግግር መንግስት ምስረታ ወዘተረፈ የፋኖን ግብ በማሰናከል የአማራን ህልውና ትግል ከአሸናፊነት ለማጨናገፍ የሚቆመር ሴራና ድራማ ነው‼️  ይህን የአማራ ህልውና መዳኛ ብቸኛ መርህ በስነ ልቦናችንና አዕምሮአችን በማስረፅ ቀጥዬ ያቀረብሁትን የማንቂያ ድዎል ተግባራዊ እናድርግ‼️ ዘመነ ካሴ እያቀፈ የሚያስተዋውቃቸው የብአዴን ልጆች እነ #አስረስ፣ #ማርሸትና ቡድናቸው በተለያየ ክፍለ አገር የሚገኙ ግብረአበሮቻቸውን አስተባብረው የፋኖ አንድነት መሰረትን ለማለት ማታለያ ድራማቸውን #በመጨረስ ላይ ይገኛሉ። ፎቶው ጸሃፊውን አይወክልም! አስረስ ማረ ዳምጤ በአስተባባሪነት የሚመራው ይሄ #የብአዴን ፋኖ ቡድን ግልፅ አላማው የፋኖ አንድነት መሰረትን በማለት #የሰላም ኮሚቴ ተብሎ በብአዴን ከተሰየመው የሰለጠኑ ካድሬዎች ስብስብ ጋር በአጠቃላይ የፋኖ አንድነት በሚመስል ስም #ለውይይትና ቀጥሎም #ለድርድር ለመሰየም አማራውን ለማታለል የሚያስችለው ሴራ የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ እንደሆነ ተደርሶበታል።  ስለዚህ መላው የአማራ ህዝብና የታጠቀው ፋኖ በሙሉ ፋኖ #4ኪሎን በመቆጣጠር ስርነቀል ለውጥ ለማወጅ የሚያደርገውን የመጨረሻ ትንቅንቅ በዋዜማው ለማሰናከል የሚሸረብ #ፀረአማራ ተልኮ አስፈላጊውን እርምጃ በመውሰድ #

ስርነቀል ለውጥ ማምጣት የአማራ ብሄርተኝነት የህልውና ትግል ብቸኛ ግብ ነው። በ Alen Kassahun

ምስሉ ጸሃፊውን አይወክልም፡፤ ከ50 አመታት በላይ የተተከለውንና በተግባር እየተፈፀመ ያለውን አማራን ማጥፋትና ኢትዮጵያን ማፍረስ ከስሩ በመንቀል #4ኪሎን ተቆጣጥሮ ስርነቀል ለውጥ ማምጣት የአማራ ብሄርተኝነት የህልውና ትግል ብቸኛ ግብ ነው። ፋኖ በሚያደርገው የህልውና ትግል አማራ ጠልነት የወለደውን የአማራን ዘር ማጥፋት፤ ማፅዳት፤ የሰባዊ መብት ጥሰትና አገር ማፍረስ አለምአቀፍ ወንጀል ከስሩ ነቅሎ ሊቀብረው #በዋዜማው ላይ እንገኛለን። ስለሆነም ፋኖ እያደረገ ያለውን የህልውና ትግል #በድል እንዳይቋጭ  በድርድር፣ በእርቅና በምክክር ሰበብ የፋኖን ድል ለመቀልበስና ለመንጠቅ ከአሜሪካ እስከ አዲስ አበባና መቀሌ ድረስ በሚሸረብ ሴራ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ፤ በስልታዊ አማራነትም ሆነ በአማራ ጠልነት የተሰለፉ ቅጥረኞች ደፋ ቀና እያሉ እንደሚገኙ ግልፅ ነው። ፋኖ #አራት ኪሎን በመቆጣጠር ስርነቀል ለውጥ ለማወጅ በድል ዋዜማ ላይ ሆኖ እያደረገ ያለውን የመጨረሻውን ትንቅንቅ ለማሰናከልና ድሉን ለመሸጥ ተቀጥራችሁ ስለ ድርድር፣ ሽግግር፣ እርቅ፣ ውይይትና በመሳሰሉ አጀንዳዎች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ እየሰሩ የሚገኙ ቅጥረኞችን ከቀጣሪዎች እኩል ማሸነፍና ማስወገድ የህልውና ትግላችን ብቻኛ አማራጭ መሆኑ ለማንም ግልፅ ሊሆን ይገባል። ስለሆነም የዜግነት ፓለቲካ አቀንቃኝ የ3ኛ ወገን ቅጥረኞችን ከጀርባው አሰልፎ የአማራን ብሄርተኝነት የማድፈቅ አጀንዳቸውን አዝሎ ከአማራ ህልውና ትግል መሀል የተገኘው #እስክንድር ነጋ ከአማራ ህልውና ትግል ጓዙን ጠቅልሎ እንዲወጣ ማድረግ ለነገ የሚባል አይደለም። የእስክንድር ነጋ #የእየሱስ ክርስቶስነት ገፀ ባህሪ በሂደት እየተገፈፈ መምጣት አማራ ጠል ሀይሎችን ወደ እቅድ ሁለት ሴራ እንዲገቡ እያስገደደ በመሆኑ የአማራ ብሄርተኛ #እስክንድር ነጋ

በጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay)

ሻለቃ ዳዊትን በተለያዩ ምክንያቶችና ወቅቶች እንደ እኔ የተቻቸው ፈልጋችሁ አታገኙም። ያ ወቅት ሌላ ፤ ዛሬ ሌላ፤- ያ ዘመን ከ2010 ዓ.ም በፊት ነው። ሰው የነበረውን መስመር አስተካክሎ ባዲስ አካሄድ ወቅቱ በሚጠይቀው ጎዳና ከተራመደ ሌላ ምን ይፈለጋል? ዛሬ ግን ሻለቃው “ኢምፖስተር” በማለት የሚጠሩት ህቡእና ግልጽ ነብሰገዳይ ቡድን አሰማርቶ ነብስን የሚቀጭና የሚሰውር <<የወያኔ የነገድ አስተዳዳር አስቀጣዩ የኦሮሙማው የጋጠወጥ ማፍያዎች መሪ>> አብይ አሕመድ ከነገሠ ወዲህ ግን “ሻለቃው” አብይ አሕመድን እንቅልፍ ካሳጡት አርበኞች አንዱ ሆነው ብቅ ብለዋል። ያንን በማድረጋቸው “ጥበብ ሳሙኤል” የተባለ የአብይ አሕመድ አለቅላቂና ፀረ አማራና የሕግ ሙያ ትምሕርተ አለበት ተብሎ የሚነገርለት (?) ጋዜጠኛ:- አብይ አሕመድን በመደገፍ በሻለቃው ላይ ያለ ዕረፍት ረዢም ጊዜ ሲዘልፋቸው ያስገረመኝ ያህል፤ ሰሞኑን ደግሞ በሻለቃ ዳዊት ወ/ልደጊዮርጊስ ላይ አዳዲስ ዘላፊዎች ብቅ ብለዋል። “ሻለቃ ሆይ! በትግሉ ውስጥ ዛሬ ይኑሩ አይኑሩ አማራውን ለመታደግ ከፍታዎትን አሳይተዋል ፤የበኩልዎን አድርገዋል ለዚህም <<በአክብሮት ባርኔጣየን አነሳለዎታለሁ፤ አንኳን ደስ አለዎት !!!!>> አርበኛ ብቅ ባለ ቁጥር ሱሪውን የሚጎትቱ ብዙ የፖለቲካ ተውሳኮች አሉ። ሻለቃው በዛው ዕደሜአቸው የሚቻላቸውን በማድረጋቸውና ከፍታቸውን በማሳየታቸው ፤ ይህን በማድረጋቸው ዓይናቸው ከቀላ ውስጥ አንዱ ወደ “ጥንት ትፋቱ” የተመለሰው፤ በቅርቡ ከወያኔም ከኦነጎችም እየተወዳደሰ መተፋፋግ የጀመረው የወያኔው አሽከር “ኤርሚያስ ለገሰ” እና ዶ/ር አምሳሉ የተባለ “ከጎንደሬዎች እጅህን አንሳ” እያለ ሲከራከረኝ የነበረው እስከ ቅርብ ጊዜ ወዲህ የአብይ አሕመድ አወዳሽ የነበ

ሻ/ቃ ዳዊት ወ/ጊወርጊስ ስለራሳቸው የጻፉት ።ከታች ያለውን የሻለቃ ዳዊት ወ/ጊዎርጊስን የግል ፅሁፍ እንመልከት ።

ሻ/ቃ ዳዊት ወ/ጊወርጊስ ስለራሳቸው የጻፉት ።  Dawit W/Giorgis የአማራ ሕዝባዊ ግንባር የውጭ ድጋፍ ሰጪ ግብረ ሀይልን እዚህ ለማድረስ ቁልፍ ሚና በመጫወቴ ደስተኝ ነኝ:: ይህንን እድል ለሰጠኝ ወደር ለሌለው ጀግና እስክንድር ነጋ ምስጋናዬን እቀርባልሁ:: ይህንን  ግዙፍ ሀላፊነት  ለመወጣት ከሚታወቀው  በላይ ያለ እረፍት ሌት  ተቀን  የሰሩትን የስራ ባልደረቦቼን እደንቃለሁ:: አመሰግናለሁ::  እኔ የስራ ሰው ነኝ:: የእወቀትም ሰው ነኝ:: ታሪካዊና ትምህርታዊ  የሆኑ አራት  መፅሀፎችም ፅፌአለሁ:: በእንግሊዝኛም በአማርኛም::አልቀረብኝም:: ቁጥራቸው በጣም ብዙ የሆኑ ምሁራዊ  ፅሁፎችን አሳትሜአለሁ::ከአውስትራሊያ አውሮፓና አሚሪካ ካናዳ የተለያዩ ሚዲያዎች ላይ  ለብዙ አመታት ቀርቤአለሁ:: ፅሁፎቼም በ CNN ሳይቀር ወጥተውልኛል::  አገልግሎቴን ግን የምመዝነው በተግባሬ ነው:: እውቀቴን  በተግባር   በማዋል የተመሰከረልኝ  ነኝ:: እውቀትና ተግባርን በማያያዝ በውትድርና ሙያ፣ በኤርትራ  አስተዳዳሪነት፣ በዲፕሎማሲ፣ በተባበሩት መንግስታትና ለተለያዪ መንግስታት በችሎታ አማካሪ ሆኜ  አገልግያለሁ::  ሰውም የሚያውቀኝ : እኔም እራሴን የማውቀው እንደ  ተግባር  ሰው ነው::እውቀቴን ለተግባሬ መሳሪያ እድርጌ የኖርኩ ከጦርሜዳ እስክ ህይወት  ማዳን ታላላቅ  ዘመቻዎች (humanitarian operations) በእውቀትና በኩራት ያገለግልኩ ነኝ:: ለኢትዮጵያ  አንድነትና ለአገሬ ህዝብ ፍቅሬን በደሜ አስመክሬአለሁ:: በውጊያ ቆስያለሁ:: አድር ባይ ሆኜ  በደርግ የፖለቲካ ሥርዓት መቆየት ስችል  ከሥርዓቱ መራቅ ብቻ ሳይሆን ወጥቼ  ስርአቱን ለማስለወጥ  ረዥምና ውስብስብ ትግል ውስጥ የነበርኩ ነኝ:: ለዚሁ ትግል በሱዳንና በኬንያ ጠረፎች አድርገን  አንዳንድ

አለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ነኝ የሚለው ቡድን ዓላማ ምንድነው ? በወንድወሰን ተክሉ

ይህ ምስል ጸሃፊውን አይወክልም! «...አማራ ለ450 ዓመታ መንፈሱ የተሰበረ ገበሮ ሕዝብ ነው..» ሀብታሙ ተገኝ (ፕ/ር) « እኔ እስክንድር  የአማራ ሕዝብ ከደረሰበት የህልውና አደጋ እኩል የሚሆን ዓላማ አለው ብዬ አላምንም» አቻምየለህ ታምሩ፤ አለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ነኝ የሚለው ቡድን ዓላማ ምንድነው ? በወንድወሰን ተክሉ እራሱን አለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ነኝ የሚለው ቡድን የዙም ውይይት ፕሮግራም ክፍል ሁለትን የተመለከተ ምልክታ:- ባለፈው  ወር ብቻ ሳይሆን ባለፈው ዓመት ዴሴምበር 2023 ( ዛሬ ጃንዋሪ 1 ቀን 2024 ነን)  እራሱን አለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ ብሎ የሚጠራው ቡድን «ጸረ አማራ ኢትዮጲያዊነት» በሚል አርእስት ስር ሀብታሙ ተገኝ (ፕ/ር) ዋና ተናጋሪ ተጋባዥ የሆነበትን  የዙም ውይይት አካሂዶ የነበረ ሲሆን የዚህ ውይይት ክፍል ሁለት  ባሳለፍነው ወር ዴሴምበር 23ቀን በማዘጋጀት አቻምየለህ ታምሩና ሀብታሙ ተገኝ (ፕ/ር) ተናጋሪ እንግዳ በማድረግ አካሂዷል። በእርግጥ  ከዚህ ከሁለተኛው የውይይት ፕሮግራም በፊት በተክሌ ይሻው በኩል የዙም ሊንክ ተልክሎኝ በሰዓት ጥበት ምክንያት መገኘት ባልችልም ዛሬ ግን በቻናላቸው ላይ የጫኑትን ይህን ክፍል ሁለት ውይይት ከተመለከትኩ በኋላ ይህን ምልክታዬን  አንባቢው ሊረዳ በሚያስችል መልኩ አንድ ሰዓት ከሰላሳ ደቂቃ የፈጀን ውይይት ይዘት በመጭመቅ እንደሚከተለው አቅርቤያለሁ። ይህ ምስል ጸሃፊውን አይወክልም! 1ኛ - ውይይቱን አዘጋጅን ማንነት በተመለከተ፦  አለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ባለፈው መስከረም ወር ላይ  በጌታቸው በየነ ሰብሳቢነት ተመሰረትኩ ብሎ እራሱን ያስተዋወቀ ሲሆን ጌታቸው በየነ ማለት ደግሞ በወቅቱ የ I AM ሰብሳቢ የነበረ እና