Skip to main content

በጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay)

ሻለቃ ዳዊትን በተለያዩ ምክንያቶችና ወቅቶች እንደ እኔ የተቻቸው ፈልጋችሁ አታገኙም። ያ ወቅት ሌላ ፤ ዛሬ ሌላ፤- ያ ዘመን ከ2010 ዓ.ም በፊት ነው። ሰው የነበረውን መስመር አስተካክሎ ባዲስ አካሄድ ወቅቱ በሚጠይቀው ጎዳና ከተራመደ ሌላ ምን ይፈለጋል? ዛሬ ግን ሻለቃው “ኢምፖስተር” በማለት የሚጠሩት ህቡእና ግልጽ ነብሰገዳይ ቡድን አሰማርቶ ነብስን የሚቀጭና የሚሰውር <<የወያኔ የነገድ አስተዳዳር አስቀጣዩ የኦሮሙማው የጋጠወጥ ማፍያዎች መሪ>> አብይ አሕመድ ከነገሠ ወዲህ ግን “ሻለቃው” አብይ አሕመድን እንቅልፍ ካሳጡት አርበኞች አንዱ ሆነው ብቅ ብለዋል።

ያንን በማድረጋቸው “ጥበብ ሳሙኤል” የተባለ የአብይ አሕመድ አለቅላቂና ፀረ አማራና የሕግ ሙያ ትምሕርተ አለበት ተብሎ የሚነገርለት (?) ጋዜጠኛ:- አብይ አሕመድን በመደገፍ በሻለቃው ላይ ያለ ዕረፍት ረዢም ጊዜ ሲዘልፋቸው ያስገረመኝ ያህል፤ ሰሞኑን ደግሞ በሻለቃ ዳዊት ወ/ልደጊዮርጊስ ላይ አዳዲስ ዘላፊዎች ብቅ ብለዋል።

“ሻለቃ ሆይ! በትግሉ ውስጥ ዛሬ ይኑሩ አይኑሩ አማራውን ለመታደግ ከፍታዎትን አሳይተዋል ፤የበኩልዎን አድርገዋል ለዚህም <<በአክብሮት ባርኔጣየን አነሳለዎታለሁ፤ አንኳን ደስ አለዎት !!!!>>

አርበኛ ብቅ ባለ ቁጥር ሱሪውን የሚጎትቱ ብዙ የፖለቲካ ተውሳኮች አሉ። ሻለቃው በዛው ዕደሜአቸው የሚቻላቸውን በማድረጋቸውና ከፍታቸውን በማሳየታቸው ፤ ይህን በማድረጋቸው ዓይናቸው ከቀላ ውስጥ አንዱ ወደ “ጥንት ትፋቱ” የተመለሰው፤ በቅርቡ ከወያኔም ከኦነጎችም እየተወዳደሰ መተፋፋግ የጀመረው የወያኔው አሽከር “ኤርሚያስ ለገሰ” እና ዶ/ር አምሳሉ የተባለ “ከጎንደሬዎች እጅህን አንሳ” እያለ ሲከራከረኝ የነበረው እስከ ቅርብ ጊዜ ወዲህ የአብይ አሕመድ አወዳሽ የነበረው “ከጠ/ቅላይ ሚኒስትሩ በታች ያሉት እንጂ እሳቸው ተገቢው ሥራቸው እየሰሩ ነው…>> እያለ አየሩን ሲየቆሽሽ የነበረው (በቅርቡ ደግሞ ከኔ አልፎ ዘመድኩን በቀለ (ነጭ ነጭዋን) ጋር የተጣመደው “ጎንደር ለጎንደሬዎች” ባዩ ዶ/ር አምሳሉ የተባለው በሻለቃው ላይ አፉን የሚከፍተውና እና ሌለው ደግሞ እንዲሁ በወያኔ ዘመን “የኦነግ ባንዴራም የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማም እኩል አሸብርቁ” እያለ ሲያውከን የነበረው ዛሬ የአብይ አሕመድ ካድሬ ሆኖ “የሃቅና ሳቅ” ዩቱብ አዘጋጅ “አበበ ቶላ” (ቶኩቻው) የተባለው እንግሊዝ አገር የሚኖሮው <<የፖለቲካ ባለጌ>> ፤ ባልተገራ ምላሱ በውትድርና እና በትምህርት እንዲሁም አገራቸውን ያገለገሉበት የውትድርና ማዕርጋቸውን በማንኳሰስ “ሹሉቃ” እያለ የመንደር ስድብ ሲዘልፋቸው መስማት እጅግ ከገረመኝ የሰሞኑ ክስተት አንዱ ነው። ሌሎችም አሉ።

ሻለቃ ዳዊትን ብቻ ሳይሆን የተጠመዱት <<ታላቁ አርበኛ እስክንድር ነጋንም>> ሳይቀር “እስክንድር ያለ ቦታው ነው የገባው፤ እዛ በረሃ ጠመንጃ ይዞ ከመታገል ይልቅ እዚህ መጥቶ ለተጋዮቹ የንዋይ (የገንዘብ) ድጋፍ ሰጪ ቢሆን የረባ አስተዋጽኦ ያደርግ ነበር>> ሲል ያደመጥኩት እጅግ የማከብረው ተመራማሪው ወጣት ምሁሩ የጥንቱ ወዳጄ <<አቻምየለህ ታምሩ>> እንዴት ወደ እዚህ ዓይነት የወረደ ግምገማ እንደገባ አስደግጦኛል። ምሁሩ ፕሮፌሰር ሃብታሙም በበኩሉ “የእስክንድር ዓላማ ምንድነው?” ሲሉ አቻምየለህ ታምሩ ጋር አብረው ጠይቋል። እስክንድር ለምን ተገፍቶ ፤ ተገፍቶ ፤ ተገፍቶ ፤ እኛ እና ጠያቂዎቹ ያልተቀበልነው መከራ የተቀበለ አስገራሚ የዘመናችን አርበኛ እስክንድር “ኣላማው ምንድነው?” ትበሎ ሲጠየቅ እውነት እስክንድር ለምን ተገፍቶ እዛ ጫካ እንደገባ ዓላማው ለምን እና ለማን ተብሎ ፍዳውን እያየ እንዳለ “ሰሚ አጥቶ ለነበረው ለአማራው ተስፋ ; መመኪያ ፤ የሞራልና የጉልበት አለኝታ እየሆነ እንደሆነ እውን ይጠፋቸዋል? ዓለማው ምንድነው!? ደጋግሞ እስክንድር ያዳመጠ ሰው እንዴት ዓላማው እስካሁን አልበራለትም? ከጥፋት ራስን መከላከል እንዴት የዓላማ ጥያቄ ያስነሳል? ወይ ከዚህ ከዲያስፖራ ምቾት ለቅቀን እዛው ጫካ እራሳችንን እናግኝ ካልሆነ “መከራቸውን እያዩ ላሉ ራሳቸውን ከመጠቃት ለማዳን የሚታገሉ ዜጎችን ጥያቄ ውስጥ ማስገባት ነውር ነው። በዙርያቸው ለግንጠላ እየሄዱ ባሉ ታጣቂዎች የተከበበው የአማራ ሕዝብና ሕዝባቸው በጥቃት ቀለበት የገባባቸው ታጋዮች፤ ዓላማቸው ምንም ይሁን ምን ለጥያቄ የሚቀርቡ አይደሉም።

እኛ በተደንደላቀቀ አልጋ ተኝተን ግማሹ እስር ቤት በካቲና ታስሮ ግማሹ በየጫካው በጥይት እየተቆላ እኛ ዩ ቱብ ላይ በጋለ ብረት በሚጠበሱ በታሰሩትና በጥይት በሚቆሉት ላይ ዓላማን ማስነሳት ዕብደት ወይስ እውቀት? እነ መስከረም አበራ እና በሺዎቹ እመጫቶች ልጆቻቸውን ጥለው በጭለማ ታስረዋል፤ እነዚህን ለማስለቀቅ በሚጥሩ አርበኞች ላይ መሳለቅና ዓላማቸውን መጠየቅ የተመቻቸው ሰዎች ጥያቄ ነው። እግዚአብሔርን እንፍራ እንጂ። እኔ ትግሬ ነኝ፤ ትግራይ ምድር ውስጥ በየአዳራሹ የሚነገረው ስለግንጠላ ነው፤ ብታደምጧቸው ትደነግጡና ዕብደት ወይስ ድንቁርና ትላላችሁ። ጉዟቸው ስለ ግንጠላ ዛቻ እንጂ ስለ አንድነት አይደለም። ኦሮሞዎቹም እንደዚያ፤ በነዚህ መሃል እንደ “ሳንድዊች” የታጠፈው ሕዝብ እንደሚዳቓ ያለ ተከላካይ ቆሞ በሁለም እቅጣጫ ይለቅ? የነዚህ ታጋዮች ዓላማ መጠየቅ ፈጣሪን የደፈርነው መስሎ አልታያችሁም?

መስክሩላቸው ብንባል <<አፋቸው ማይክሮፎን ላይ መትከል እንጂ “ተግዳሮትን” (ቻለንጅን) መቋቋም የማይችሉትን እንደ እነ ኤርምያስ ለገሰ እና የፖለቲካ ባለጌው “አበበ ተላ” (ቶኪቻው) በሻለቃውና በእስክንድር ትግል ላይ “ከስራ መልስ የድብርታቸው ማስወገጃ በማድረግ” በየዩቱቡ ተድጠው የነዚህ ሰዎች ትግልና ማዕረጋቸውን ማብጠልጠል ስናደምጥ ‘ዩ ቱብ’ የሚባለው እጅግ ሲበዛ የፖለቲካ ባለጌዎችን የልብ ልብ ሰጥቷቸው በታጋዮች ላይ ሲቀልዱ ማድመጥ እውነትም <<ኢትዮጵያ አገሬ መኝ ነሽ ተላላ የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ በላ>> የሚባለው እውነት ነው።

Comments

Popular posts from this blog

"ከአሁን በሆላ ፋኖ ወደ አንድነት መምጣት አለባቸው የሚባለው አካሄድ አይሰራም" :: በወዳጄ/ቤተ አማራ ወሎ

ከአሁን  በሆላ  ፋኖ  ወደ  አንድነት    መምጣት  አለባቸው  የሚባለው  አካሄድ  አይሰራም::  ክህደት   ከተፈፀመ  በሆላ  አንዱ  ቡድን  ከሌላው  ስር  ሆኖ  ይቀጥላል  ማለት  የማይቻል   ነው::  ምክኒያቱም 1ኛ:- 27  ቀን  ቁጪ  ብለው   መክረዋል :: እያንዳንዱ  አደረጃጄት  ሰነድ  ፅፈው  አቅርበዋል::  በቀረበው  ሰነድ  ላይ  ከፍተኛ  ውይይት  ተደርጎበት  የሚወድቀው  ወድቆ  የሚፈለገው  ፀድቋል::ቃለ  መሀላ  ፈፅመው   ወደ  ምርጫ   ለመግባት  ተስማምተዋል:: እጃቸውን  አውጥተው   ከመረጡ  በሆላ    ግን    "ጨዋታ  ፈረሰ  ዳቦ  ተቆረሰ"   የሚል  የህፃን  ልጂ  ጨዋታ  ውስጥ  መግባት   የአማራን  ህዝብም  ሆነ  የፋኖን  ትግል  መናቅ  ነው:: ይህ  አልበቃ  ብሎ   "ምርጫው  ከኛ  እውቅና  ውጪ  ነው  እኛ  አናውቀውም"  የሚል   የውሸት    የህፃን  ልጂ  ፕሮፓጋንዳ...

የጋራ ጠላታችንን ልናሸንፈው የምንችለው ብአንድነት ብቻ ነው:: ሻ/ቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ

ከዚህ መከፋፈል ነፃ ሆነን ፊትለፊት  እየወረረ : እየገደለን: ያለውን የጋራ ጠላታችንን ልናሸንፈው የምንችለው ብአንድነት ብቻ ነው:: ሻ/ቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ ሻ/ቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ በምናየው  ታላቅ  የፋኖ ትግል የዲያስፓራ ትልቁ ስራ ገንዘብ መስብስብ ነው:: እሱም እየቀዘቀዘ ሄዷል:: ጦርነቱን ያራዝምነው እኛው ነን:: ይህ ደግሞ ትልቁና ዋናው የጠላት ስትራተጂ ነው:: ጦርነቱን ማራዘምና ከአማራ ምድር እንዳይወጣ በማድረግ: ፋኖን በመከፋፈል አዳክመዋለሁ ! እበትነዋለሁ ! የሚል የአቢይ አህመድ ትልቁ  የወቅቱ ስትራተጂ መሆኑን ተረድተናል::: በዚህም ምክንያት በአጠረ ጊዜ  ሊጠናቀቅ የሚችለውን  ትግል  ዲያስፓራ በምቀኝነት: በቅናት: በሌለ  ስልጣን  ላይ በመፋተግ: በተቀጣሪነት: በጠባብ አስተሳስብ: ትግላችንን ወደኋላ  በመጎተትና  እንዲራዘም ብሎም እንዲዳከም በማድረግ ታሪካዊ ወንጀል እየስራ ነው:: ከዚህ መከፋፈል ነፃ ሆነን ፊትለፊት  እየወረረ : እየገደለን: ያለውን የጋራ ጠላታችንን ልናሸንፈው የምንችለው በአንድነት ብቻ ነው::  አሸናፊነት ትብብርና  የጋራ ስትራተጂ ይጠይቃል:: የተግባር ዲያስፓራ እንሁን:: አማራን እንደ  ህዝብ ኢትዮጵያንም እንደ ሀገር  ለማዳን  ዋናው መሳሪያችን  አንድነት ነው:: በውስጣችን ያለውን ልዩነት በመጠቀም  አገራችንን ለማጥፋት: በአካባቢያችን  ያለውን የሀይል አሰላለፍ ስንመለከት ፍፁም ፍፁም  አደገኛ  መሆኑን እንገነዘባለን:: በዲያስፓራ  መጨቃጨቅና መዘላለፍ  እንደ ባህልና እንደ ትልቅ   የጦርነት ስትራተጂ ተደር...

አለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ነኝ የሚለው ቡድን ዓላማ ምንድነው ? በወንድወሰን ተክሉ

ይህ ምስል ጸሃፊውን አይወክልም! «...አማራ ለ450 ዓመታ መንፈሱ የተሰበረ ገበሮ ሕዝብ ነው..» ሀብታሙ ተገኝ (ፕ/ር) « እኔ እስክንድር  የአማራ ሕዝብ ከደረሰበት የህልውና አደጋ እኩል የሚሆን ዓላማ አለው ብዬ አላምንም» አቻምየለህ ታምሩ፤ አለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ነኝ የሚለው ቡድን ዓላማ ምንድነው ? በወንድወሰን ተክሉ እራሱን አለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ነኝ የሚለው ቡድን የዙም ውይይት ፕሮግራም ክፍል ሁለትን የተመለከተ ምልክታ:- ባለፈው  ወር ብቻ ሳይሆን ባለፈው ዓመት ዴሴምበር 2023 ( ዛሬ ጃንዋሪ 1 ቀን 2024 ነን)  እራሱን አለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ ብሎ የሚጠራው ቡድን «ጸረ አማራ ኢትዮጲያዊነት» በሚል አርእስት ስር ሀብታሙ ተገኝ (ፕ/ር) ዋና ተናጋሪ ተጋባዥ የሆነበትን  የዙም ውይይት አካሂዶ የነበረ ሲሆን የዚህ ውይይት ክፍል ሁለት  ባሳለፍነው ወር ዴሴምበር 23ቀን በማዘጋጀት አቻምየለህ ታምሩና ሀብታሙ ተገኝ (ፕ/ር) ተናጋሪ እንግዳ በማድረግ አካሂዷል። በእርግጥ  ከዚህ ከሁለተኛው የውይይት ፕሮግራም በፊት በተክሌ ይሻው በኩል የዙም ሊንክ ተልክሎኝ በሰዓት ጥበት ምክንያት መገኘት ባልችልም ዛሬ ግን በቻናላቸው ላይ የጫኑትን ይህን ክፍል ሁለት ውይይት ከተመለከትኩ በኋላ ይህን ምልክታዬን  አንባቢው ሊረዳ በሚያስችል መልኩ አንድ ሰዓት ከሰላሳ ደቂቃ የፈጀን ውይይት ይዘት በመጭመቅ እንደሚከተለው አቅርቤያለሁ። ይህ ምስል ጸሃፊውን አይወክልም! 1ኛ - ውይይቱን አዘጋጅን ማንነት በተመለከተ፦  አለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ባለፈው መስከረም ወር ላይ  በጌታቸው በየነ ሰብሳቢነት ተመሰረትኩ ብሎ እራሱን ያስተዋወቀ ሲ...