Skip to main content

"ከአሁን በሆላ ፋኖ ወደ አንድነት መምጣት አለባቸው የሚባለው አካሄድ አይሰራም" :: በወዳጄ/ቤተ አማራ ወሎ

ከአሁን  በሆላ  ፋኖ  ወደ  አንድነት    መምጣት  አለባቸው  የሚባለው  አካሄድ  አይሰራም::  ክህደት   ከተፈፀመ  በሆላ  አንዱ  ቡድን  ከሌላው  ስር  ሆኖ  ይቀጥላል  ማለት  የማይቻል   ነው::  ምክኒያቱም

1ኛ:- 27  ቀን  ቁጪ  ብለው   መክረዋል :: እያንዳንዱ  አደረጃጄት  ሰነድ  ፅፈው  አቅርበዋል::  በቀረበው  ሰነድ  ላይ  ከፍተኛ  ውይይት  ተደርጎበት  የሚወድቀው  ወድቆ  የሚፈለገው  ፀድቋል::ቃለ  መሀላ  ፈፅመው   ወደ  ምርጫ   ለመግባት  ተስማምተዋል:: እጃቸውን  አውጥተው   ከመረጡ  በሆላ    ግን    "ጨዋታ  ፈረሰ  ዳቦ  ተቆረሰ"   የሚል  የህፃን  ልጂ  ጨዋታ  ውስጥ  መግባት   የአማራን  ህዝብም  ሆነ  የፋኖን  ትግል  መናቅ  ነው:: ይህ  አልበቃ  ብሎ   "ምርጫው  ከኛ  እውቅና  ውጪ  ነው  እኛ  አናውቀውም"  የሚል   የውሸት    የህፃን  ልጂ  ፕሮፓጋንዳ   እንዲሰራጪ  አድርገዋል::ከዚህ  በሆላ   ይህ  ቡድን  የታላቁ  እና  የጠቢቡ   የአማራ  ህዝብ  መሪ  ነኝ    ብሎ   አይኑን   በጨው   አጥቦ  ለመምጣት  እንዴትስ  ይደፍራል ????  

የድምጽ ቅንብሩ ጸሃፊውን አይወክልም።


 2ኛ:- የፋኖ  ወታደራዊ  ጦር  ዋና  አዛዢ   የሆነው  ሻለቃ  ዝናቡ  የራሳቸውን   ድክመት  እና  ሴራ  በአማራ  ህዝብ  ላይ  ለማሸከም   የአማራን  ህዝብ  በጂምላ    ይህ   "ጎጃም  ጠልነት  ነው"   ብሎ  ከወነጄለ  በሆላ   ይቅርታ  ሳይጠየቅበት   በጋራ  ለአንድ  አላማ  እንዴትስ     መስራት  ይቻላል???  የአማራ   ጪምብላቸውን  አውልቀው  እንዴትስ  በመቅፅበት  ወደ  ጎጣቸው   ተወርውረው  ሊገቡ  ቻሉ???  አጄንዳቸው   እንዴትስ  የጎጥ  አጄንዳ  ሊሆን  ቻለ??? ወደ  ትግሉ  የገቡትስ  ለጎጥ  አላማ  ነወይ??  

 3ኛ:-  ይህ  ቡድን  በዲያስፖራ   ቃል  አቀባያቸው   አማክይኚነት    ሚስተር  X ካልተመረጠ   አማራነታችንን  እንተዋለን    በማለት  የጎጃምን  አማራ  ከሌላው  ወንድሞቹና  እህቶቹ  ለመለየት  ከፍተኛ  ስራ  ከተሰራ  በሆላ   እንዴት  አብሮ  መስራት  ይቻላል??

 4ኛ:-   ከሰፈራቸው  ውጪ  ያለውን  አማራ   መጤ  :  ሰፋሪ  :  አማራዊ  ስነ  ልቦና  የሌለው  : በመጤ  አንመራም  :  የሚል  ፋሺስታዊ     ፕሮፖጋንዳ    ከተሰራጨ  በሆላ  እንደ  አማራ  ከዚህ  ፋሺስት  ቡድን  ጋር  በጋራ   መቀጠል  ይቻላል  ወይ???

የወሎ/ ቤተ አማራ ;  የጎንደር :  የሸዋ ;  እና  30 ሚልዮን  ከክልሉ  ውጪ  የተወለደን  አማራ  መጤ  ነው  የአማራ  ስነልቦና  የለውም  በነሱ  አንመራም  ያለን  አካል  እንዴትስ  አንደ  አማራ   መቀበል  ይቻላል???? ይህ  ባእዴናዊ  እና   ኦነጋዊ  አካሄድ  አይደለም  ወይ??  ከሰፈሬ  ውጪ  ያለውን  አማራ  የምንታገልለት  ሳይሆን  የምንታገለው  ነው  ማለትስ  አይደለም ወይ??? ይህ  ብአዴናዊ  መርህ  ለምን  ተፈለገ???  

 ይህ  ፋሺስት  ቡዲን   ሌላውን  የአማራ    ህዝብ  እኛና  እነሱ ብሎ  identify   እድርጎ  አስቀምጧል::  ይህ  ማለት  already  የመጄመሪያውን   የጄኖሳይድ    መስፈርት  አሞልተዋል:: ይህ  ቡድን  እድሉን  ቢያገኝ  እኛና  እነሱ  ብሎ  identify ያደረገውን  አካል  ነው    መጄመሪያ  የሚያጠፋው::   ከአብይ  አህመድ  ኦነጋዊ  ኦሮሙማ  የዳነውን  አማራ   እንደገና  በዚህ  ፋሺስት  ቡድን  ላለመጥፋት  ምን  ጋራንቲ  አለን???? ይሰመርበት  ይህን  ፋሺስታዊ   አካሄድ  በቃላሉ  አናየውም  በቀላሉ  አናልፈውም!!!!

በመሆኑም    ይህ  ቡድን   በአማራ  ህዝብ  ላይ  ቀላል  የማይበል  የስነ  ልቦና  ቀውስ    አድርሷል    እርስ  በርሱ  እንዲወዛገቡ  አድርጏል:: በአስራጨው  ውዢንብር  እና  ፋሺስታዊ    ንግግር    መሰረት   በማህበረሰባችን    ላይ  ብዙ   ጉዳት  ደርሷል:: የስነ  ልቦና  ቀውስ  አስከትሎል::  ***** ይህን   የስነ  ልቦና  ቀውስ  ለመጠግን   የአማራን  ህዝብ   በይፋ  ይቅርታ  በመጠየቅ    ልብ  የሚያሞቅ  ሁሉንም  የአማራ  ህዝብ  አንድ  የሚያደርግ  speech ማድረግ    አለበት::

 ይቅርታ  ከተጠየቀ    እና  የህዝባችንን  አንድነት  ካረጋገጥን  በሆላ   የመጣንበትን  የትግል  ጉዞ  ገምግመን ሁለቱ  አደረጃጄቶች  በጋራ  ለመስራት   የጋራ  ስትራቴጂክ  መንደፍ  ያስፈልጋል::

Comments

Popular posts from this blog

ዐማራን ወክሎ ከወያኔ ጋር ስለሰላምም ሆነ ስለትጥቅ ትግል አልፎም ስለመንግሥት መሥረታ መነጋገር ፈጽሞ አይቻልም

ዐማራን ወክሎ ከወያኔ ጋር ስለሰላምም ሆነ ስለትጥቅ ትግል አልፎም ስለመንግሥት መሥረታ መነጋገር ፈጽሞ አይቻልም፤ ዐማራ የተጨፈጨፈው በሦስት ዓመት ዕድሜ ውስጥ ብቻ አይደለም። በ17 ዓመት የወያኔ የሽፍተነት ዘመን፣ 27 ዓመት የወያኔ የመንግሥትነት ዘመን ወደኋላ ተጨምሮ ነው። ከውያኔ ጋር ሰላምን ወይም ትጥቅ ትግልን እናደርጋለን የሚሉ ሁሉ ውሾች ናቸው። "ውሻ ወደ ትፋቱ ይመለሳል" በምሣሌ 26፤11 እና 2ኛ ጴጥሮስ2፤22 የተጠቀሰውን መጽሐፋዊ ዘገባ በማንበብ ከውያኔ ጋር የመከሩትን የውሾች ባህሪ ለይቶ መረዳት ነው። ምስሉ ጸሃፊውን አይወክልም 1ኛ. የዐማራን ሕዝብ የመደብ ጠላት አድርጎ ወያኔን በደደቢት የመሠረተውና 17 ዓመት በትጥቅ ትግል 27 ዓመት በመንግሥትነት በደምሩ 44 ዓመት ከሰባት ሚሊዮን በላይ ዐማራን ሕዝብ ያለማቋረጥ ያስጨፈጨፈ፣ ርስቱን የነጠቀ በጀምላ የገደለ ያፈናቀለ፣ የትግራይን ሕዝብ ከኢትዮጵያዊ ቀዳሚ ሕዝብነቱና ማንነቱ ያስከዳ ስብሐት ነጋ ፤   2ኛ. ከዐማራ ሕዝብ ይልቅ የሱዳን ሕዝብ ይሻለናል ብሎ በማይካድራ በጭና ዐማራን በከፍተኛ መራር በሆነ ጭካኔ ያስጨፈጨፈው፣ በመጨረሻ ተረጋግቶ መኖር ሲችል ዕቅድና ዓላማ በሌለው ጦርነት አንድ ሚሊዮን የትግራይ ወጣት ያስጨፈጨፈ፣ የትግራይን ሕዝብም ሆነ የዐማራን ሕዝብ አዘቅት ውስጥ የከተተ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ፤   3ኛ. የወያኔ ተሿሚ ሆኖ የዐማራን መሬት ፀገዴና ጠገዴ እያለ እየከፋፈለ ለወያኔ ያስረከበ፣ የግጨውን መሬት ለወያኔ በችሮታ ፈርሞ የሰጠ፤ እነ ዶክተር አባቸው ለማስገደል ቅድመ ሁኔታዎችን ከአመቻቸ በኋላ ወደ አሜሪካ ሀገር ሾልኮ ወጥቶ ከተገደሉ በኋላ ተመልሶ ጥቁር ለብሶ የዓዞ እንባ ሲያነባ ሲመጻደቅ የነበረ የሕወሀትም ሆነ የብልጽግና ቀንደኛና ፊ...

በጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay)

ሻለቃ ዳዊትን በተለያዩ ምክንያቶችና ወቅቶች እንደ እኔ የተቻቸው ፈልጋችሁ አታገኙም። ያ ወቅት ሌላ ፤ ዛሬ ሌላ፤- ያ ዘመን ከ2010 ዓ.ም በፊት ነው። ሰው የነበረውን መስመር አስተካክሎ ባዲስ አካሄድ ወቅቱ በሚጠይቀው ጎዳና ከተራመደ ሌላ ምን ይፈለጋል? ዛሬ ግን ሻለቃው “ኢምፖስተር” በማለት የሚጠሩት ህቡእና ግልጽ ነብሰገዳይ ቡድን አሰማርቶ ነብስን የሚቀጭና የሚሰውር <<የወያኔ የነገድ አስተዳዳር አስቀጣዩ የኦሮሙማው የጋጠወጥ ማፍያዎች መሪ>> አብይ አሕመድ ከነገሠ ወዲህ ግን “ሻለቃው” አብይ አሕመድን እንቅልፍ ካሳጡት አርበኞች አንዱ ሆነው ብቅ ብለዋል። ያንን በማድረጋቸው “ጥበብ ሳሙኤል” የተባለ የአብይ አሕመድ አለቅላቂና ፀረ አማራና የሕግ ሙያ ትምሕርተ አለበት ተብሎ የሚነገርለት (?) ጋዜጠኛ:- አብይ አሕመድን በመደገፍ በሻለቃው ላይ ያለ ዕረፍት ረዢም ጊዜ ሲዘልፋቸው ያስገረመኝ ያህል፤ ሰሞኑን ደግሞ በሻለቃ ዳዊት ወ/ልደጊዮርጊስ ላይ አዳዲስ ዘላፊዎች ብቅ ብለዋል። “ሻለቃ ሆይ! በትግሉ ውስጥ ዛሬ ይኑሩ አይኑሩ አማራውን ለመታደግ ከፍታዎትን አሳይተዋል ፤የበኩልዎን አድርገዋል ለዚህም <<በአክብሮት ባርኔጣየን አነሳለዎታለሁ፤ አንኳን ደስ አለዎት !!!!>> አርበኛ ብቅ ባለ ቁጥር ሱሪውን የሚጎትቱ ብዙ የፖለቲካ ተውሳኮች አሉ። ሻለቃው በዛው ዕደሜአቸው የሚቻላቸውን በማድረጋቸውና ከፍታቸውን በማሳየታቸው ፤ ይህን በማድረጋቸው ዓይናቸው ከቀላ ውስጥ አንዱ ወደ “ጥንት ትፋቱ” የተመለሰው፤ በቅርቡ ከወያኔም ከኦነጎችም እየተወዳደሰ መተፋፋግ የጀመረው የወያኔው አሽከር “ኤርሚያስ ለገሰ” እና ዶ/ር አምሳሉ የተባለ “ከጎንደሬዎች እጅህን አንሳ” እያለ ሲከራከረኝ የነበረው እስከ ቅርብ ጊዜ ወዲህ የአብይ አሕመድ አወዳሽ የነበ...

"ምኗ ላይ ተቀምጣ በሽንቷ ሰፌድ ትሰፋላች":- አዲሱ የአቢይ ካቢኔ አሰያዬም ፤ በሸንቁጥ አየለ

ችግሩ ያለዉ የጎሳ ፖለቲካ ርዕዮተ ፍልስፍናዉ ላይ ነዉ::ኢትዮጵያዉያንን ሀገር አልባ ያደረገዉን የጎሳ ፖለቲካ ፍልስፍና መሰረት ላይ የቆመ ካቢኔ ምንም አይነት መልካም ግለሰቦችን ሰብስብቦ ቢያቅፍ ከቶም የሀገር መድሃኒት አያመጣም:: ሆኖም የዚህ ስርዓት የጥቅም ተጋሪዎች እና እግር አጣቢዎች ይሄን የጎሳ ፖለቲካ አስተሳሰብ የተለያዬ የማስመሰያ መቀባቢያ በመቀባት ጸረ ሰዉ የሆነዉን የጎሳ ፖለቲካ አስተሳሰብ ለማስቀጠል እና ህዝብን ለማምታታት ብዙ ሲዳክሩ ይሰተዋላል::በአዲሱ የአቢይ ካቢኔ አሰያዬም የተከናወነዉ ድራማም ይሄዉ ነዉ:: እከሌ ከኦህዴድ:እከሌ ከብአዴን:እንትና ከአብን : እንቶኔ ከኢዜማ: እንቶኔ ደግሞ ከትግራይ ብልጽግና ተሾሙ እያሉ ብዙ የጥቅም ተጋሪዎች እና የአገዛዙ ሚዲያ ብዙ ይቀባጥራሉ::በደስታም እንኳን ደስ አለህ ይባባላሉ::ኢትዮጵያዉያን ግን አሁንም ሀገር አልባ ናቸዉ:: የኢትዮጵያ የችግር ምንጭ ሁሉ አንድ ነዉ::ይሄዉም የጎሳ ፖለቲካ ፍልስፍና ነዉ::መለስ ዜናዊ የሀገሪቱን ጥፋት ያመጣዉ የጎሳ ፖለቲካ ፍልስፍና በማራመድ ነበር::መለስ ዜናዊ ጠቅላይ ሚኒስቴር ሆኖ በስሩ ብዙ በግለሰብ ደረጃ መጥፎ የማይባሉ ሰዎችን በካቢኔዉ ዉስጥ ሰግስጎ ነበር:: ሆኖም የመለስ ዜናዊ ካቢኔ እያንዳንዱ የሚመራበት መርህ በጎሳ ፖለቲካ ፍልስፍና እና ቀመር ስለሆነ የሚሰሩ ስራዎች ሁሉ በዚሁ መርዛማ ህሳቤ ዙሪያ የሚሽከረከሩ ነበሩ:: አሁንም አቢይ የሾማቸዉ ሰዎች መጥፎ ናቸዉ ጥሩ ናቸዉ የሚለዉ አይደለም ጥያቄዉ:: ወይም ደግሞ ሰዎች ከዬትኛዉ ፓርቲ ተመርጠዉ ተሾሙ አይደለም ጥያቄዉ:: አቢይ የሚመራበትም የፖለቲካ ፍልስፍና እንደ መለስ ዜናዊ ሁሉ የጎሳ ፖለቲካ ፍልስፍና ነዉና ያዉ ዉሃ ቢወቅጡት እንቦጭ ነዉ::ስለዚህ የተሿሚዎቹ መልካምነት ወይም የመጡበት የፓርቲ ቁም ነገ...