Skip to main content

የጋራ ጠላታችንን ልናሸንፈው የምንችለው ብአንድነት ብቻ ነው:: ሻ/ቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ

ከዚህ መከፋፈል ነፃ ሆነን ፊትለፊት  እየወረረ : እየገደለን: ያለውን የጋራ ጠላታችንን ልናሸንፈው የምንችለው ብአንድነት ብቻ ነው:: ሻ/ቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ

ሻ/ቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ

በምናየው  ታላቅ  የፋኖ ትግል የዲያስፓራ ትልቁ ስራ ገንዘብ መስብስብ ነው:: እሱም እየቀዘቀዘ ሄዷል:: ጦርነቱን ያራዝምነው እኛው ነን:: ይህ ደግሞ ትልቁና ዋናው የጠላት ስትራተጂ ነው:: ጦርነቱን ማራዘምና ከአማራ ምድር እንዳይወጣ በማድረግ: ፋኖን በመከፋፈል አዳክመዋለሁ ! እበትነዋለሁ ! የሚል የአቢይ አህመድ ትልቁ  የወቅቱ ስትራተጂ መሆኑን ተረድተናል::: በዚህም ምክንያት በአጠረ ጊዜ  ሊጠናቀቅ የሚችለውን  ትግል  ዲያስፓራ በምቀኝነት: በቅናት: በሌለ  ስልጣን  ላይ በመፋተግ: በተቀጣሪነት: በጠባብ አስተሳስብ: ትግላችንን ወደኋላ  በመጎተትና  እንዲራዘም ብሎም እንዲዳከም በማድረግ ታሪካዊ ወንጀል እየስራ ነው::

ከዚህ መከፋፈል ነፃ ሆነን ፊትለፊት  እየወረረ : እየገደለን: ያለውን የጋራ ጠላታችንን ልናሸንፈው የምንችለው በአንድነት ብቻ ነው:: 

አሸናፊነት ትብብርና  የጋራ ስትራተጂ ይጠይቃል:: የተግባር ዲያስፓራ እንሁን:: አማራን እንደ  ህዝብ ኢትዮጵያንም እንደ ሀገር  ለማዳን  ዋናው መሳሪያችን  አንድነት ነው:: በውስጣችን ያለውን ልዩነት በመጠቀም  አገራችንን ለማጥፋት: በአካባቢያችን  ያለውን የሀይል አሰላለፍ ስንመለከት ፍፁም ፍፁም  አደገኛ  መሆኑን እንገነዘባለን::

በዲያስፓራ  መጨቃጨቅና መዘላለፍ  እንደ ባህልና እንደ ትልቅ   የጦርነት ስትራተጂ ተደርጎ ተይዞአል:: ይህንን አይነት የጦርነት ስትራተጂ  ከአማራ  ዲያስፓራ  ውጭ  በታሪክም ባለንበት ጊዜም የትም  አለም ተስምትም አያውቅም:: ለብዙዎች መዝናኛ: መሳቂያና መሳለቂያ ሆኗል:: አማራ ህልውናውን ለማስጠበቅ በፋኖ አማካኝነት በታላቅ መስዋዕትነት የሚደረገው የአማራ የህልውና ትግል ምን የፓለቲካ ፍልስፍና  ያስፈልገዋል ? አላማችን ግልፅ ነው:: የፋኖ ሰራዊት ትግል ይህንን አላማ  በሙያና በመሳሪያ ተደግፎ : ራሱ በመረጠው በመሰረቱት ከእሱ ጋር ተሰልፈው እዚህ ካደረሱት መሪዎቹ ጋር  አዲስ አበባ ገብቶ ሁሉን አቃፌ የሆነ ጊዚያዊ መንግስት ማቋቋም ነው:: ይህ ነው ፍልስፍናው:: ስለ ጊዚያዊ መንግስትና አገራዊ መረጋጋት: ከዚያም በኋላ መፈፅም ስላለባቸው ሁሉ የፓለቲከኞች ሀላፊነት ነው:: እነሱ ስራቸውን ይጀምሩ:: የተጀመሩም አሉ:: በፋኖ ሰራዊት የህልውና ትግል ጣልቃ አንግባ:: 

ይህ ባለመሆኑ ምክንያት  ከእውነተኛው  አለም እርቀን የራሳችን የሆነ የማሸነፍ ሳይሆን በታኝ የሆነ አጥፊ ባህል እያስፋፋን ነው:: በዚህም ምክንያት በአገርም በውጭም ያሉ ጠላቶቻችን ወጥመድ ውስጥ አውቀንም ሳናውቅውም እየገባን ነው:: ይህንንም እውነታ  ለመቀበል  የብዙዎች  አዕምሮ  ተመርዟል:: ብዙ ጊዜ ጥቃት በተለይ የዘር ማጥፋት ወንጀሎች: ተጠቂ ህዝብን አንድ ያደርጋል:: ያሰባስበዋል:: የእነዚህ ወንጀሎች ሰለባ የሆነው ሀገር ቤት ያለው ህዝባችን አንድ ነው:: ድጋፍ ሊሰጠው የሚችለው ከአብራኩ የወጣው በዲያፓራ ያለው ብዙው የአማራ ህዝብ ግን አንድ አይደለም:: ይህ አንድ አለመሆን ዲያስፓራ አማራን ምን ነካህ ያስብለዋል? በህግም በሞራልም በእምነትም : ጠይቁ ራሳችሁን::

ከከፋፋይ  አጀንዳ  ለመራቅና በመሀከላችን  ያሉ ጠላቶቻችንን ለይተን አውቀን አቸናፊ ሆነን እንድንወጣ  አንድ እንሁን:: ትግላችን ከግለስቦች በላይ ነው:: የመሪ እጦት የለብንም:: ፋኖዎቻችችን ከምንገምተው በላይ ደረጃ  በደረጃ   እያደጉ በወታደራዊ ሙያዎችና በጠቅላላ የፖለትካ  እውቀት መሪዎች እየወለዱ እዚህ አድርሰውናል:: እምነታችን በግለሰቦች ሳይሆን በፋኖ ላይ ብቻ ይሁን:: አማራ የተሸከመው ሀላፊነት የአማራን ህልውና ማስጠበቅ ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያም እንደ ሀገር እንድትቀጥል ነው:: የ120 ሚሊዮን ህዝብ ህልውና ከአማራ ህልውና ጋር  የተያያዘ ነው:: የአማራ ህልውና የሚከበረው በተረጋጋች ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ ነው:: ፓለቲከኞች ከጎን ሆናችሁ  እርዱት::

ከላይ አትጫኑበት:: ይህንን ሳንገነዘብ የመከፋፈል አጀንዳችንን ብንቀጥልበት ለሚያስከትለው ውድቀት በመጀመሪያ ረድፍ ተጠያቂው የአማራ ዲያስፓራ ነው::

Comments

Popular posts from this blog

ዐማራን ወክሎ ከወያኔ ጋር ስለሰላምም ሆነ ስለትጥቅ ትግል አልፎም ስለመንግሥት መሥረታ መነጋገር ፈጽሞ አይቻልም

ዐማራን ወክሎ ከወያኔ ጋር ስለሰላምም ሆነ ስለትጥቅ ትግል አልፎም ስለመንግሥት መሥረታ መነጋገር ፈጽሞ አይቻልም፤ ዐማራ የተጨፈጨፈው በሦስት ዓመት ዕድሜ ውስጥ ብቻ አይደለም። በ17 ዓመት የወያኔ የሽፍተነት ዘመን፣ 27 ዓመት የወያኔ የመንግሥትነት ዘመን ወደኋላ ተጨምሮ ነው። ከውያኔ ጋር ሰላምን ወይም ትጥቅ ትግልን እናደርጋለን የሚሉ ሁሉ ውሾች ናቸው። "ውሻ ወደ ትፋቱ ይመለሳል" በምሣሌ 26፤11 እና 2ኛ ጴጥሮስ2፤22 የተጠቀሰውን መጽሐፋዊ ዘገባ በማንበብ ከውያኔ ጋር የመከሩትን የውሾች ባህሪ ለይቶ መረዳት ነው። ምስሉ ጸሃፊውን አይወክልም 1ኛ. የዐማራን ሕዝብ የመደብ ጠላት አድርጎ ወያኔን በደደቢት የመሠረተውና 17 ዓመት በትጥቅ ትግል 27 ዓመት በመንግሥትነት በደምሩ 44 ዓመት ከሰባት ሚሊዮን በላይ ዐማራን ሕዝብ ያለማቋረጥ ያስጨፈጨፈ፣ ርስቱን የነጠቀ በጀምላ የገደለ ያፈናቀለ፣ የትግራይን ሕዝብ ከኢትዮጵያዊ ቀዳሚ ሕዝብነቱና ማንነቱ ያስከዳ ስብሐት ነጋ ፤   2ኛ. ከዐማራ ሕዝብ ይልቅ የሱዳን ሕዝብ ይሻለናል ብሎ በማይካድራ በጭና ዐማራን በከፍተኛ መራር በሆነ ጭካኔ ያስጨፈጨፈው፣ በመጨረሻ ተረጋግቶ መኖር ሲችል ዕቅድና ዓላማ በሌለው ጦርነት አንድ ሚሊዮን የትግራይ ወጣት ያስጨፈጨፈ፣ የትግራይን ሕዝብም ሆነ የዐማራን ሕዝብ አዘቅት ውስጥ የከተተ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ፤   3ኛ. የወያኔ ተሿሚ ሆኖ የዐማራን መሬት ፀገዴና ጠገዴ እያለ እየከፋፈለ ለወያኔ ያስረከበ፣ የግጨውን መሬት ለወያኔ በችሮታ ፈርሞ የሰጠ፤ እነ ዶክተር አባቸው ለማስገደል ቅድመ ሁኔታዎችን ከአመቻቸ በኋላ ወደ አሜሪካ ሀገር ሾልኮ ወጥቶ ከተገደሉ በኋላ ተመልሶ ጥቁር ለብሶ የዓዞ እንባ ሲያነባ ሲመጻደቅ የነበረ የሕወሀትም ሆነ የብልጽግና ቀንደኛና ፊ...

በጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay)

ሻለቃ ዳዊትን በተለያዩ ምክንያቶችና ወቅቶች እንደ እኔ የተቻቸው ፈልጋችሁ አታገኙም። ያ ወቅት ሌላ ፤ ዛሬ ሌላ፤- ያ ዘመን ከ2010 ዓ.ም በፊት ነው። ሰው የነበረውን መስመር አስተካክሎ ባዲስ አካሄድ ወቅቱ በሚጠይቀው ጎዳና ከተራመደ ሌላ ምን ይፈለጋል? ዛሬ ግን ሻለቃው “ኢምፖስተር” በማለት የሚጠሩት ህቡእና ግልጽ ነብሰገዳይ ቡድን አሰማርቶ ነብስን የሚቀጭና የሚሰውር <<የወያኔ የነገድ አስተዳዳር አስቀጣዩ የኦሮሙማው የጋጠወጥ ማፍያዎች መሪ>> አብይ አሕመድ ከነገሠ ወዲህ ግን “ሻለቃው” አብይ አሕመድን እንቅልፍ ካሳጡት አርበኞች አንዱ ሆነው ብቅ ብለዋል። ያንን በማድረጋቸው “ጥበብ ሳሙኤል” የተባለ የአብይ አሕመድ አለቅላቂና ፀረ አማራና የሕግ ሙያ ትምሕርተ አለበት ተብሎ የሚነገርለት (?) ጋዜጠኛ:- አብይ አሕመድን በመደገፍ በሻለቃው ላይ ያለ ዕረፍት ረዢም ጊዜ ሲዘልፋቸው ያስገረመኝ ያህል፤ ሰሞኑን ደግሞ በሻለቃ ዳዊት ወ/ልደጊዮርጊስ ላይ አዳዲስ ዘላፊዎች ብቅ ብለዋል። “ሻለቃ ሆይ! በትግሉ ውስጥ ዛሬ ይኑሩ አይኑሩ አማራውን ለመታደግ ከፍታዎትን አሳይተዋል ፤የበኩልዎን አድርገዋል ለዚህም <<በአክብሮት ባርኔጣየን አነሳለዎታለሁ፤ አንኳን ደስ አለዎት !!!!>> አርበኛ ብቅ ባለ ቁጥር ሱሪውን የሚጎትቱ ብዙ የፖለቲካ ተውሳኮች አሉ። ሻለቃው በዛው ዕደሜአቸው የሚቻላቸውን በማድረጋቸውና ከፍታቸውን በማሳየታቸው ፤ ይህን በማድረጋቸው ዓይናቸው ከቀላ ውስጥ አንዱ ወደ “ጥንት ትፋቱ” የተመለሰው፤ በቅርቡ ከወያኔም ከኦነጎችም እየተወዳደሰ መተፋፋግ የጀመረው የወያኔው አሽከር “ኤርሚያስ ለገሰ” እና ዶ/ር አምሳሉ የተባለ “ከጎንደሬዎች እጅህን አንሳ” እያለ ሲከራከረኝ የነበረው እስከ ቅርብ ጊዜ ወዲህ የአብይ አሕመድ አወዳሽ የነበ...