Skip to main content

ከትግራዩ ትህነግ ጋር አብረን እንሰራለን፤ ከጎጃሙ አማራ፤ የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድትጅት በጎጃም እዝ ጋር ግን አብረን አንሰራም፤ የገቡበት ገብተን የማያዳግም እርምጃ እንወስድባቸዋለን ....አስረስ ማረ ዳምጤ ፤ በወንድወሰን ተክሉ

ከትግራዩ ትህነግ ጋር አብረን እንሰራለን፤ ከጎጃሙ አማራ፤ የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድትጅት በጎጃም እዝ ጋር ግን አብረን አንሰራም፤ የገቡበት ገብተን የማያዳግም እርምጃ እንወስድባቸዋለን ....አስረስ ማረ ዳምጤ

በጎጃም ምድር ተሸሽጎ ከትህነግ ጋር እየተባበረ በጎጃም ምድር በተወለዱ ፋኖዎቻችን ላይ የሚዘምትን ውስጣዊን ጠላት መንጥረን ማጽዳት አለብን ‼️‼️‼️

ምስሉ ጸሃፊውን አይወክልም።


በወንድወሰን ተክሉ

አስረስ ማረ ዳምጤ - የአማራ ፋኖ በጎጃም ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ  የትህነጉ መሪ ዶ/ር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል በቅርቡ ከአማራ ፋኖ እና ከኤርትራው መንግስት ሻእቢያ ጋር አብረን ለመስራት እንፈልጋለን ለሚለው ገለጻው በብርሃን ፍጥነት ብቅ ብሎ «ከህወሃት ጋር አብረን እንሰራለን» በማለት ምላሽ ሰጥቷል፡፡ ይህ የአስረስ ማረ ዳምጤ ምላሽ የአንድ ግለሰብ ሳይሆን የድርጅቱ፤ ማለትም የአማራ ፋኖ በጎጃም ተብሎ የሚጠራ አንድ አደገኛ ተዋጊ ቡድን ድርጅታዊ አቌም መሆኑን መላው የአማራ ህዝብና መላው የአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች በሙሉ ሊያውቁት የሚገባ እውነታ ነው፡፡

በእርግጥ የትህነጉ ዶ/ር ደብረጺዮን ከፋኖ ጋር አብሮ ለመስራት እንፈልጋለን የሚለው አሁናዊ አባባል ዝም ብሎ ከመሬት ተነስቶ የተነገረ ሳይሆን በሁለቱ ፋሺስታዊ ቡድኖች መካከል - ማለትም በዘመነ ካሴ በሚመራው የአማራ ፋኖ በጎጃም እና በዶ/ር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል በሚመራው የትግራዩ ትህነግ መካከል በተካሄደ ምስጢራዊ ግንኙነትና ስምምነት  መሰረት ዛሬ ዶ/ር ደብረጺዮን በአደባባይ የተናገሩት ሀቅ መሆኑን ማወቅና መረዳት ይገባል፡፡

ባለፈው ሀምሌ ወር ውስጥ የአማራ ፋኖ በጎጃም አመራር ነን የሚሉት አስረስ ማረ እና ማርሸት ጸሀዬ ከትግራዩ ትህነግ ከዶ/ር ደብረጺዮን ጋር ምስጢራዊ ንግግርና ድርድር ማድረጋቸውን ያጋለጥ የድምጽ ሪኮርድ ይፋ ማድረጋችን ይታወሳል፡፡

በዚያ ምስጢራዊ የስልክ ንግግር አስረስና ማርሸት ከደብረጽዮን ጋር ምስጢራዊ ንግግር፤ድርድርና ስምምነት ማድረጋቸውን በመግለጽ ከጌታቸው ረዳ ጋር ይቀረናል በማለት በሁለቱ ቡድኖች መካከል በአካል ተገናኝተው ጉዳዪን ለመቌጨት የመገናኛ ስፍራ፤ቦታና ግዜ በመምረጥ ላይ መሆናቸውን ሲገልጹ የሰማንበት አውዲዮ ሲሆን ያ ማለት  በዘመነ ካሴ የሚመራው የአማራ ፋኖ በጎጃም የሚባለው ቡድን ከጎጃም ህዝብ፤ከአማራ ህዝብና ከመላው የአማራ ፋኖ ሀይሎች የተደበቀን ምስጢራዊን ግንኙነትን እና ስምምነትን ከትግራዩ ትህነግ ጋር ማድረጉን ያረጋግጥልናል፡፡

ከዚህ ምስጢራዊ ግንኙነትና ስምምነትና አንጻ ወያኔ በወልቃይት ጠገዴ፤ ጠለምትና በሰሜን ወሎ ራያ በኩል የትንኮሳ ወረራ በከፈተችበት ወቅት - ባለፈው ሰኔ ወር- የአማራ ፋኖ በጎጃም ቃለ አቀባይ ማርሸት ጸሀዬ በሚዲያ ብቅ ብሎ ወያኔ ተሳስታ ብትወረን እና ጦርነት ብትከፍትብን እንኳን እኛ መልሰን አንተኩስባትም በማለት  በሁለቱ ፋሺስታዊ ቡድኖች  መካከል መላው የአማራ ህዝብና መላው የአማራ ፋኖ ያለወቀው ምስጢራዊ ስምምነት መደረጉን ያረጋገጥንበት ክስተት ብለን መዝገበነዋል፡፡ ስለሆነም ይህንን ድብቅ ምስጢራዊ ግንኙነትና ስምምነትን መሰረት በማድረግ ባለፈው ሳምንት ዶ/ር ደብረጺዮን ከፋኖ ጋር ለመስራት ዝግጁ ነን ብሎ ሲናገር በብርሃን ፍጥነት ብቅ ብሎ የማረጋገጫውን ቃል አዎን ከህወሃት ጋር አብረን እንሰራለን የሚለውን ማረጋገጫ በአስረስ ማረ ዳምጤ አንደበት ሲነገር ለመስማት የበቃነው፡፡

💥 በዘመነ ካሴ የሚመራው የአማራ ፋኖ በጎጃም  ከትህነግ ጋር ምን ሰጥቶ ምን በመቀበል ነው ምስጢራዊ ስምምነትን ለማድረግ የቻለው ??

ሁለቱ ቡድኖች ዝም ብሎ በነጻ አብሮ ለመስራት ተስማምተዋል ብሎ የሚያስብ አማራ ካለ ለአቅመ ፖለቲካ ያልደረሰ እንጭጭ ብቻ ሆኖ እናገኛለን፡፡ በፖለቲካው አለም ጥቅም አልባ ስምምነትና አጋርነት ፈጽሞ የለም፡፡ ምስጢራጺም ሆኑ ግልጽ ይፋዊ ስምምነቶች በሙሉ ሰጥቶ በመቀበል ላይ የተመሰረተ በመሆኑ ሁለቱ ፋሺስቶች ማለትም በዘመነ የሚመራው የሽፍታ ቡድን እና በዶ/ር ደብረጺዮን የሚመራው ትህነግ በኩል የተስማሙበት የሰጥቶ መቀበል ሁኔታ ምንድነው ብለን እንድንጠይቅ ያደርገናል፡፡ በዘመነ ካሴ የሚመራው ቡድን እራሱን በአማራ ስምና በአማራ ፋኖ ጎጃም ስም  ሰይሞ ከህወሃት ጋር ሲደራደር ምን ለመስጠት ተስማምቶ ነው?? ከህወሃትስ ምን ለማግኘት ቃል ተገብቶለት ነው??

የወልቃይት ጠገዴ የራያ ጉዳይ የእኛ ችግር አይደለም በማለት ለሚታወቀው ዘመነ ካሴና ግብረ አበሮቹ ከህወሃት ጋር ለመስማማት በገጸ በረከትነት አሳልፎ የሰጠው የእነዚህኑን አማራዊያንን ማንነትና ግዛት ለትግራዩ ትህነግ አሳልፎ በመስጠት የተደረገ ስምምነት ሲሆን በትህነግ በኩል ወታደራዊ ትጥቅና ሎጀስቶክስ በምትኩ በማቅረብ ዘመነንና ቡድኑን የአማራ ክልል ገዢ የማድረግ የአቅም ግንባታ ለማቅረብ እንደተስማሙ ነው ከደረሰን ልዩ መረጃ ማወቅ የቻልነው፡፡ ሆኖም ይህንን ምስጢራዊ ስምምነቱን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል የመላው አማራ ፋኖ መሪነትን በእጁ ማስገባት ባለመቻሉ ክፉኛ ስጋትና ንዴት ላይ ያለው የዘመነ ካሴ ቡድን በዶ/ር ደብረጺዮን በኩል ከፋኖ ጋር ለመስራት ዝግጁ ነን የምትለዋን ቃል እንደሰማ በብርሃን ፍጥነት ብቅ ብሎ አዎን ከትህነግ ጋር አብረን ለመስራት ዝግጁ ነን በሚል ምላሽ ማረጋገጫ ለመስጠት እንደተገደደ ነው ማረጋገጥ የቻልነው፡፡

አንዳንድ የዋህ አማሮች፤ በተለይም ለህልውና ትግሉ ቀና አመለካከት ያላቸው አማሮች የአስረስ ማረ ዳምጤን ከህወሃት ጋር እንሰራለን ያለበትን ከአንከር ሚዱያ ጋር ያደረገውን ውይይት በአድናቆት ሲያስተጋቡት ታዝበናል፡፡  በመሰረቱ አስረስ ማረ ዳምጤ ከአንከሩ አዘጋጅ መሳይ መኮንን ጋር ባደርገው ቃለ ምልልስ የፖለቲካ ብስለቱን ያሳየበት ውይይት ሳይሆን ለጎጃም አማራ ያልገለጸውን ድብቅ የፖለቲካ ሴራን ያነገበ መርዘኛነቱን ያጋለጠበት ውይይት ሆኖ ነው ያየነው፡፡

የአንድ የበሰለ ፖለቲካ ፍልስፍናን አራማጅ ሰው ቀዳሚ  ተግባር የሚሆነው ከማይጎራበተው እና አማራን በጠላትነት ከፈረጀ የጠላት ሀይል ጋር ተቀራርቦ ለመሰራት ያለውን ቁርጠኝነትን በመግለጽ ሳይሆን እታገልለታለሁ የሚለውን ህዝብ ጥቅምና  ፍላጎትን በማስጠበቅ ደረጃ የማያወላውል ቁርጠኛ አቌምና አላማ እንዳለው በመግለጽ ነው መሆን ያለበት፡፡

አባቶቻችን ከእሩቅ ካለ መልዓክ ጎረቤትህ ያለው ሰይጣን ይቀርብሃል፤ ይጠቅምሀል ሲሉ ይደመጣሉ፡፡ ፈረንጆች ደግሞ ከማያውቁት መልዓክ  የሚያውቁት ሰይጣን ይሻላል ሲሉ ይገልጻሉ፡፡ ዘመነ ካሴ፤ አስረስ ማረ ዳምጤ፤ ዝናቡ ልንገረውና መሰሎቹ  ጎጃምና ወሎን ተሻግረው የአማራን ህዝብ በማንነቱ በጠላትነት ከፈረጀው የትግራዪ ትህነግ ጋር አብሮ ለመስራት የሚያበቃ ምስጢራዊ ስምምነት ከማድረግ ይልቅ በጎጃም ምድር ካለው አቻ ወንድማቸው የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት የጎጃም እዝ ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችል ስነልቦና እና አስተሳሰብ ይኖራቸው ይገባ ነበር፡፡

ድንበር ተሻግሮ ከአማራ ጠላት ጋር የሚደረግ ስምምነትና ግንኙነት ለአማራ ህዝብ ጥቅም ታስቦ ቢሆን ኖሮ ድንበር ተሻግሮ ከጠላት ጋር ለመስራት የቌመጠ አማራ ነኝ ባይ ቡድን በአብሮ አደጉ የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት የጎጃም እዝ አመራርና አባላት ላይ ጦርነት ባልከፈተ ነበር፡፡

ስለሆነም የዘመነ ካሴና የአስረስ ማረ ከህወሃት ጋር አብሮ ለመሰራት ዝግጁ ነን መግለጫ ያረጋገጠልን ምስጢራዊው ስምምነት በአማራ ህዝብ ዋጋ ከፋይነት በእኛ በአማራ ህዝብ ላይ የተፈጸመ ደባ መሆኑን ነው የሚያሳየን እንጂ ለአማራ ጥቅም ተብሎ የተደረገ ስምምነት አለመሆኑን ነው፡::



Comments

Popular posts from this blog

"ከአሁን በሆላ ፋኖ ወደ አንድነት መምጣት አለባቸው የሚባለው አካሄድ አይሰራም" :: በወዳጄ/ቤተ አማራ ወሎ

ከአሁን  በሆላ  ፋኖ  ወደ  አንድነት    መምጣት  አለባቸው  የሚባለው  አካሄድ  አይሰራም::  ክህደት   ከተፈፀመ  በሆላ  አንዱ  ቡድን  ከሌላው  ስር  ሆኖ  ይቀጥላል  ማለት  የማይቻል   ነው::  ምክኒያቱም 1ኛ:- 27  ቀን  ቁጪ  ብለው   መክረዋል :: እያንዳንዱ  አደረጃጄት  ሰነድ  ፅፈው  አቅርበዋል::  በቀረበው  ሰነድ  ላይ  ከፍተኛ  ውይይት  ተደርጎበት  የሚወድቀው  ወድቆ  የሚፈለገው  ፀድቋል::ቃለ  መሀላ  ፈፅመው   ወደ  ምርጫ   ለመግባት  ተስማምተዋል:: እጃቸውን  አውጥተው   ከመረጡ  በሆላ    ግን    "ጨዋታ  ፈረሰ  ዳቦ  ተቆረሰ"   የሚል  የህፃን  ልጂ  ጨዋታ  ውስጥ  መግባት   የአማራን  ህዝብም  ሆነ  የፋኖን  ትግል  መናቅ  ነው:: ይህ  አልበቃ  ብሎ   "ምርጫው  ከኛ  እውቅና  ውጪ  ነው  እኛ  አናውቀውም"  የሚል   የውሸት    የህፃን  ልጂ  ፕሮፓጋንዳ...

የጋራ ጠላታችንን ልናሸንፈው የምንችለው ብአንድነት ብቻ ነው:: ሻ/ቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ

ከዚህ መከፋፈል ነፃ ሆነን ፊትለፊት  እየወረረ : እየገደለን: ያለውን የጋራ ጠላታችንን ልናሸንፈው የምንችለው ብአንድነት ብቻ ነው:: ሻ/ቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ ሻ/ቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ በምናየው  ታላቅ  የፋኖ ትግል የዲያስፓራ ትልቁ ስራ ገንዘብ መስብስብ ነው:: እሱም እየቀዘቀዘ ሄዷል:: ጦርነቱን ያራዝምነው እኛው ነን:: ይህ ደግሞ ትልቁና ዋናው የጠላት ስትራተጂ ነው:: ጦርነቱን ማራዘምና ከአማራ ምድር እንዳይወጣ በማድረግ: ፋኖን በመከፋፈል አዳክመዋለሁ ! እበትነዋለሁ ! የሚል የአቢይ አህመድ ትልቁ  የወቅቱ ስትራተጂ መሆኑን ተረድተናል::: በዚህም ምክንያት በአጠረ ጊዜ  ሊጠናቀቅ የሚችለውን  ትግል  ዲያስፓራ በምቀኝነት: በቅናት: በሌለ  ስልጣን  ላይ በመፋተግ: በተቀጣሪነት: በጠባብ አስተሳስብ: ትግላችንን ወደኋላ  በመጎተትና  እንዲራዘም ብሎም እንዲዳከም በማድረግ ታሪካዊ ወንጀል እየስራ ነው:: ከዚህ መከፋፈል ነፃ ሆነን ፊትለፊት  እየወረረ : እየገደለን: ያለውን የጋራ ጠላታችንን ልናሸንፈው የምንችለው በአንድነት ብቻ ነው::  አሸናፊነት ትብብርና  የጋራ ስትራተጂ ይጠይቃል:: የተግባር ዲያስፓራ እንሁን:: አማራን እንደ  ህዝብ ኢትዮጵያንም እንደ ሀገር  ለማዳን  ዋናው መሳሪያችን  አንድነት ነው:: በውስጣችን ያለውን ልዩነት በመጠቀም  አገራችንን ለማጥፋት: በአካባቢያችን  ያለውን የሀይል አሰላለፍ ስንመለከት ፍፁም ፍፁም  አደገኛ  መሆኑን እንገነዘባለን:: በዲያስፓራ  መጨቃጨቅና መዘላለፍ  እንደ ባህልና እንደ ትልቅ   የጦርነት ስትራተጂ ተደር...

አለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ነኝ የሚለው ቡድን ዓላማ ምንድነው ? በወንድወሰን ተክሉ

ይህ ምስል ጸሃፊውን አይወክልም! «...አማራ ለ450 ዓመታ መንፈሱ የተሰበረ ገበሮ ሕዝብ ነው..» ሀብታሙ ተገኝ (ፕ/ር) « እኔ እስክንድር  የአማራ ሕዝብ ከደረሰበት የህልውና አደጋ እኩል የሚሆን ዓላማ አለው ብዬ አላምንም» አቻምየለህ ታምሩ፤ አለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ነኝ የሚለው ቡድን ዓላማ ምንድነው ? በወንድወሰን ተክሉ እራሱን አለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ነኝ የሚለው ቡድን የዙም ውይይት ፕሮግራም ክፍል ሁለትን የተመለከተ ምልክታ:- ባለፈው  ወር ብቻ ሳይሆን ባለፈው ዓመት ዴሴምበር 2023 ( ዛሬ ጃንዋሪ 1 ቀን 2024 ነን)  እራሱን አለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ ብሎ የሚጠራው ቡድን «ጸረ አማራ ኢትዮጲያዊነት» በሚል አርእስት ስር ሀብታሙ ተገኝ (ፕ/ር) ዋና ተናጋሪ ተጋባዥ የሆነበትን  የዙም ውይይት አካሂዶ የነበረ ሲሆን የዚህ ውይይት ክፍል ሁለት  ባሳለፍነው ወር ዴሴምበር 23ቀን በማዘጋጀት አቻምየለህ ታምሩና ሀብታሙ ተገኝ (ፕ/ር) ተናጋሪ እንግዳ በማድረግ አካሂዷል። በእርግጥ  ከዚህ ከሁለተኛው የውይይት ፕሮግራም በፊት በተክሌ ይሻው በኩል የዙም ሊንክ ተልክሎኝ በሰዓት ጥበት ምክንያት መገኘት ባልችልም ዛሬ ግን በቻናላቸው ላይ የጫኑትን ይህን ክፍል ሁለት ውይይት ከተመለከትኩ በኋላ ይህን ምልክታዬን  አንባቢው ሊረዳ በሚያስችል መልኩ አንድ ሰዓት ከሰላሳ ደቂቃ የፈጀን ውይይት ይዘት በመጭመቅ እንደሚከተለው አቅርቤያለሁ። ይህ ምስል ጸሃፊውን አይወክልም! 1ኛ - ውይይቱን አዘጋጅን ማንነት በተመለከተ፦  አለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ባለፈው መስከረም ወር ላይ  በጌታቸው በየነ ሰብሳቢነት ተመሰረትኩ ብሎ እራሱን ያስተዋወቀ ሲ...