Skip to main content

Posts

አለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ነኝ የሚለው ቡድን ዓላማ ምንድነው ? በወንድወሰን ተክሉ

ይህ ምስል ጸሃፊውን አይወክልም! «...አማራ ለ450 ዓመታ መንፈሱ የተሰበረ ገበሮ ሕዝብ ነው..» ሀብታሙ ተገኝ (ፕ/ር) « እኔ እስክንድር  የአማራ ሕዝብ ከደረሰበት የህልውና አደጋ እኩል የሚሆን ዓላማ አለው ብዬ አላምንም» አቻምየለህ ታምሩ፤ አለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ነኝ የሚለው ቡድን ዓላማ ምንድነው ? በወንድወሰን ተክሉ እራሱን አለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ነኝ የሚለው ቡድን የዙም ውይይት ፕሮግራም ክፍል ሁለትን የተመለከተ ምልክታ:- ባለፈው  ወር ብቻ ሳይሆን ባለፈው ዓመት ዴሴምበር 2023 ( ዛሬ ጃንዋሪ 1 ቀን 2024 ነን)  እራሱን አለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ ብሎ የሚጠራው ቡድን «ጸረ አማራ ኢትዮጲያዊነት» በሚል አርእስት ስር ሀብታሙ ተገኝ (ፕ/ር) ዋና ተናጋሪ ተጋባዥ የሆነበትን  የዙም ውይይት አካሂዶ የነበረ ሲሆን የዚህ ውይይት ክፍል ሁለት  ባሳለፍነው ወር ዴሴምበር 23ቀን በማዘጋጀት አቻምየለህ ታምሩና ሀብታሙ ተገኝ (ፕ/ር) ተናጋሪ እንግዳ በማድረግ አካሂዷል። በእርግጥ  ከዚህ ከሁለተኛው የውይይት ፕሮግራም በፊት በተክሌ ይሻው በኩል የዙም ሊንክ ተልክሎኝ በሰዓት ጥበት ምክንያት መገኘት ባልችልም ዛሬ ግን በቻናላቸው ላይ የጫኑትን ይህን ክፍል ሁለት ውይይት ከተመለከትኩ በኋላ ይህን ምልክታዬን  አንባቢው ሊረዳ በሚያስችል መልኩ አንድ ሰዓት ከሰላሳ ደቂቃ የፈጀን ውይይት ይዘት በመጭመቅ እንደሚከተለው አቅርቤያለሁ። ይህ ምስል ጸሃፊውን አይወክልም! 1ኛ - ውይይቱን አዘጋጅን ማንነት በተመለከተ፦  አለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ባለፈው መስከረም ወር ላይ  በጌታቸው በየነ ሰብሳቢነት ተመሰረትኩ ብሎ እራሱን ያስተዋወቀ ሲሆን ጌታቸው በየነ ማለት ደግሞ በወቅቱ የ I AM ሰብሳቢ የነበረ እና

ግርማ የሺጥላ => የኦሮሙማው መንግሥት "The New Pearl Harbor" (የመጨረሻው ክፍል) በ Dave Dawit

(Grand operation requires either grand cause or grand pretext‼‼‼) 2. Opportunity፦  ብአዴናዊውና የኦሮሙማ ፋሽስታዊ መንግሥት ተላላኪው ግርማ የሺጥላ በአብይ አህመድ በኩል በተደረገ ምደባ ከፍተኛ ጥበቃ ከሚካሄድላቸው ሹመኞች መካከል አንዱ ነው። በመሆኑም በዚህ ባንዳ ላይ ግድያ የመፈፀም ዕድል ሊኖረው የሚችል አካል፦  ሀ. Highly guarded የሆነን አካል የ security detail surpass ሊያደርግ የሚችል የ ambush drill የሰለጠነ፤ በተለይም በ killing zone መረጣ፣ after attack የ escaping route ዝግጅት፣ target የተደረገው አካል ሊገኝበት በሚችልበት ተሽከርካሪና አጠቃላይ እንቅስቃሴ የተሟላ የኢንተሊጀንስ እና insider information ያለው፣ ከግርማ የሺጥላ የግልና convoy guards ለሚሰነዘርበት የ counter ambush ጥቃት በተኩስና በስልት የበላይነት መያዝ የሚችል በዚህ የ ambush technique ስልጠናም የካበተ ስልጠናና ልምድ ያለው አካል ሊሆን ሲገባው፥ በዚህ ረገድ ተሳዳጁ የአማራ ወጣት በዚህ መጠን Centralized በሆነ የኢንተለጀንስ እና ወታደራዊ አደረጃጀት ባልተቋቋመበት ሁኔታ፣ የግርማ የሺጥላን security shield penetrate አልያም surpass አድርጎ ይህንን ይፈፅማል ማለት ከእውነታና ከአመክንዮ ጋር መጣላት ነው።  * ወደ ቀጣዩ ነጥብ ከማምራታችን በፊት ከቦታው በደረሰን መረጃ መሠረት የዕለቱ የዚህ ብአዴናዊ ሹመኛ የ security detail ምን እንደሚመስል እንመልከት።  ግርማ የሺጥላ ወደ ሰሜን ሸዋ ሲንቀሳቀስ በአራት አይነት መኪኖች በመታጀብ ነበር፦  1. አብይ አህመድ "የልዩ ጥበቃ ብርጌድ" በማለት

ግርማ የሺጥላ => የኦሮሙማው መንግሥት "The New Pearl Harbor" በ Dave Dawit

(Grand operation requires either grand & noble cause or grand pretext‼‼‼) * 32ኛው የአሜሪካ ፕሬዝደንት ዴልኖ ሩዝቬልትና የፔንታገን የጦር አማካሪዎቻቸው በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት በፓስፊክ ውቅያኖስ Pearl harbor የነበረው የአሜሪካ የባህር ኃይል ቤዝ ለጥቃት የተጋለጠ መሆኑን ከማወቅም በላይ በዚያ ልክ ተጋላጭ እንዲሆን ያደረጉት ሆን ብለው ነበር። ከዚያም ተሻግረው በ double agent ሰላዮቻቸው አማካኝነት መረጃው ለጃፓን አመራሮች እንዲደርስም አድርገዋል። የሚፈለገው አላማ ጃፓን ጥቃት እንድትሰነዝርና፥ "ራስን ከጥቃት ለመከላከል" በሚል ሽፋን የአሜሪካን ህዝብ ጎትተው ጦርነት ውስጥ ለመክተት ነበር፥ ያም ተሳካላቸው። * በ ማርች 1998 ዓ.ም የኢራቁ ፕሬዝደንት ሳዳም ሁሴን የአሜሪካን ጆሮ ጭው የሚያደርግ ዜና ይዞ ብቅ አለ። የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክርቤት በኢራቅ ለአስር ዓመታት ጥሎት የነበረው የነዳጅ ሽያጭ ማዕቀብ እየተገባደደ በመሆኑ ማዕቀቡ ሲነሳ ኢራቅ ራሷን ከPetro-Dollar system እንደምታወጣና ሽያጩንም በሌሎች ሀገራት currency እንደምታደርግ ሳዳም ገለፁ። ይህ የሳዳም መግለጫ በአሜሪካ global dominance ላይ የተቃጣ አደገኛ ጥቃትና ይዞት የሚመጣው መዘዝም ከባድ በመሆኑ ዋይት ኋውስ፣ ማንሀተንና ፔንታገን በር ዘግቶ መከረ። መክሮም ሲጨርስ ሳዳም መወገድ ብቻ ሳይሆን ኢራቅም ለሌሎች የ Petro-Dollar እስረኛ የገልፍ ሀገራት መማሪያ መሆን አለባት። ይህንን ለማድረግ ደግሞ grand and noble cause አልያም grand pretext ያስፈልጋል። የመጀመሪያውን ማግኘት ስለማይቻል ብቸኛው አማራጭ የአሜሪካዊያንን እና የአለምን ህዝብ ልብና

ኢትዮጵያ አትፈርስም እያሉ በተጨባጭ ግን እያፈረሷት ነው፤ በዶ/ር ሽፈራዉ ገሰሰ

ምስሉ ጸሃፊውን አይወክልም! ኢትዮጵያ ማለት አገር ናት፣ አንድ አገር ደግሞ አገር ለመባል መሬቱ፣ ጫካው፣ ወንዙ፣ ሸንተረሩ፣ ባህሩ፣ ሀይቁ፣ ተራራው፣ ሜዳው፣ደጋው፣ ቆላው፣ ወይናደጋው፣ በረሀው በጠቅላላው መልክዓምድሩ ብቻ ሳይሆን ሌሎች ብዙ ነገሮችን ያጠቃልላል። አገር ሲባል መሬቱ፣ ውሃ ሀብቱ፣ አየሩ፣ ሉዓላዊነቱ ብቻ ሳይሆን ዋነኛው በውስጡ የሚኖረው የአገሪቱ ባለቤት የሆነው ህዝብ ባህሉ፣ ቋንቋው፣ ወጉ፣ ልማዱ፣ ሃይማኖቱ፣ታሪኩ፣ ሰንደቅ አላማው፣ ብሔራዊ መዝሙሩ፣ መለያ አርማው፣ስርዓተ መንግሥቱ፣ አንድነቱ ስርዓተ ትምህርቱ፣ ስነ ጥበቡ፣ ስነ ህንፃው፣ ታሪካዊ ቅርሶቹ፣ ማህበራዊ መስተጋብሩ፣ ብሔራዊ በዓላቱ፣ ጀግኖቹ፣ የጦር ድሎቹ፣ የነፃነትተጋድሎ ታሪኩ፣ ምግብና የምግብ ስርዓቱ፣ኢኮኖሚው ወዘተ የሚያጠቃልል ነው። ኢትዮጵያ የብዙ ሺህ አመታት ስርዓተ መንግሥት ያላት፣ በቅኝ ያልተገዛች ከዓለማችን ቀደምት ስልጣኔወች ካላቸው ጥቂት አገሮች ውስጥ አንዷ ስትሆን በአሁኑ ወቅት ግን ከፍተኛ አደጋ ውስጥ ትገኛለች። ጠቅላይ ሚኒስቴሩን ጨምሮ ሌት ከቀን በሚዲያ እየወጡ ኢትዮጵያ አትፈርስም እያሉ እየለፈፉ በተቃራኒው ግን አገሪቱን እንመራለን ብለው የተሰየሙ ባለስልጣኖች፣ የእነርሱ አላማ ተባባሪ የሆኑ የፓለቲካ ድርጅቶችና ሌሎች አደረጃጀቶች በጋራ በመሆን በተጨባጭ ኢትዮጵያን እያፈረሷት ይገኛሉ። እየሆነ ያለውን ከላይ ከዘረዘርኳቸው የአገር ምልክቶች ውስጥ ጥቂቶቹን ወስጀ ለማሳየት እሞክራለሁ። ሉዓላዊነት አንድ ሉዓላዊ ወይም ነፃ የሆነ አገር የራሱ የሆነ በዓለም አቀፍ ህግ የታወቀ የየብስ የባህርና የአየር ክልል አለው። ይህ አገር ከሚሰጠው ፈቃድ በስተቀር በማንኛውም አገር ወይም አገሮች ሊደፈር ወይም ሊጣስ አይችልም። ነገር ግን በአሁኑ ሰዓት የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት በሰሜን ምዕራብ

ኪራላይሶን…!

 በዘመድኩን በቀለ "…ሲላ ዱኤ ጂራ… ትላለች ሴቷ ተናጋሪ… ሞቷል እኮ ነው የምትለው። ከሞተ በኋላ ለምን እንዲህ ማድረግ አስፈለገ? የሚል ድምፀት ያለው ቃል ነው የምታሰማው በኦሮሚኛ። …ዐማራ ገዳዩ የአብይ ሽመልስ ሸኔ ደግሞ አስከሬን ላይ ቆሞ ያላግጣል። ሌላኛው ደግሞ የሞተው ዐማራ አስከሬን ፊት ላይ ድንጋይ ይጭንበታል። "…ቪድዮ ቀራጩም እንዲህ ይላል። ሲንሙሊሱ… ማለትም አላሳይህም። መልክህን እንዲታይ አላደረኩም ነው የሚለው። አስከሬኑ ላይ የቆመው ባለ ጊዜም እንዲህ ይላል። ረኮን ኢንጂሩ። ችግር የለም። ብታይስ ምን ሊመጣ? ከሳሽ የለ? ጠያቂ የለ? ጊዜው እኮ የእኛ ነው እንደማለት ነው።  "…አስተውላችሁ ከሆነ አቢይ አሕመድ ሥልጣን ላይ ከወጣ ጊዜ ጀምሮ የኦርቶዶክስ በዓላትን ጠብቆ አሰቃቂ አረመኔያዊና ጭካኔ የተመላበትን ዘግናኝ ድርጊት ይፈጽማል። በዓለ መስቀልን፣ ጥምቀትን፣ ስቅለትን፣ ትንሣኤን፣ ዕርገትንም ጠብቆ እንዲሁ ነው። በወይራ ጢስ የመጣ አጋንንታም የጠንቋይ የዲያብሎስ የግብር ልጇ ስለሆነ ኦርቶዶክሳውያን በዓልን ተረጋግተው አሳልፈው አያውቁም። እስከመቼ እንዲህ እንደሚቀጥል ግን አላውቅም። "…ይሄን ዘግናኝ ጭፍጨፋ ለመቀልበስ፣ ያለፍርድም አልሞትም ማለት ለዐማራው አይፈቀድለትም። በሰሜን ሸዋ በጅብውኃ በኦሮሞ ሸኔ የተጨፈጨፉት ዐማሮች አስከሬን እስከአሁን አልተነሣም። መከላከያ በስፍራው ቢኖርም ድርጊቱን አይቃወምም። ሕዝቡም አስከሬን እንዳያነሣ ተከልክሏል። ይሄ ማለት ዐማሮች ይሄን እያዩ የሚያድናቸው ፓርቲ፣ የሚታደጋቸው መሪ ድርጅትም እንደሌላቸው ዐውቀው ሰጥ ለጥ ብለው በባርነት እንዲገዙ አልያም ያለ ከልካይ በዚህ መልክ እንደሚጨፈጭፉት መልእክት ለማስተላለፍ ነው። የእግዚአብሔር በቀል ግን ይከተላል።  • ዛሬ ለዐማራ

ስለ አቤል እንጂ ስለ ሶምሶን አናለቅስም

ግራፊክ ምስል ዴቭ ዳዊት Dave Dawit /We are a voice for unprotected civilian Amharas, Not for the willing servant of the fascistic Regime * በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከተጠቀሱት ታሪኮች የአቤልና የሶምሶን ታሪክ፥ አሁናዊውን የአማራ ፖለቲካ ሁኔታ ይገልፀዋል። አቤል የተገደለው በየዋህነት ወንድሙ ቃየንን አምኖ ወደ መገደያ ሜዳ በመውጣቱ፣ የሞት አደጋ እንደሚደርስበት የሚያውቅበት አንዳችም precedence አለመኖሩና ራሱን የሚከላከልበት አንዳችም ነገር በእጁ ባለመኖሩ ነው። በግፍ የፈሰሰው የአቤል ደም፥ በኢምፓየሯ ኢትዮጵያ በየቀኑ እየፈሰሰ የሚገኘው የብዙ ሺህ ንፁሐን አማራዎች ተምሳሌት ነው። በአንፃሩ ሶምሶን ከውልደቱ ጀምሮ የእግዚአብሔር ኃይል ያረፈበት ብርቱ ተዋጊ ነበር። ነገር ግን ሶምሶን በአመንዝራይቱ ደሊላ ፍቅር የተሸነፈ ሰውም ነበር። የሶምሶንን የኃይል ምስጢር ለማወቅ አመንዝራይቱ ደሊላ በአማላይ የሽንገላ ቃላቶች ሶምሶንን አታልላ ትጥቁን አስፈታችው። በመጨረሻም ሶምሶን በአመንዝራይቱ ደሊላ ጭን ላይ እንደተኛ ትጥቁን በፈታበት ሁኔታ (የኃይሉ ምስጢር የነበረውን ፀጉሩን ደሊላ በጭኗ ላይ አስተኝታ ላጭታው ስለነበር) በባላንጦቹ ፍልስጤማውያን እጅ ተያዘ። ከዚያ በኋላ ያለው የሶምሶን ታሪክ የባርነትና የውርደት ሞት ነው። "የአማራ ልዩ ኃይልም" የሶምሶንን የውድቀትና የውርደት ጉዞ አንድ ብሎ ጀምሯል። ትጥቁን አስረክቦ ለፋሽስቱ የኦሮሙማ መንግስት ዙፋን ጠባቂ የመሆን ተስፋ ሰንቆ ሲጓዝ፥ የአመንዝራይቱ ደሊላ ምሳሌ የሆነው ፋሽስታዊው የኦሮሙማ መንግሥት ስልሣ የልዩ ሀይል አባላትን በጅምላ ገድሏቸዋል። ይህ የውርደትና የቁልቁለት ጉዟቸው ጅማሬ እንጂ ፍፃሜያቸው አይደለም‼‼‼ መሣሪያውን

The Anti Semitic stand of the OLF : Speech at the Jerusalem Center for Public Affairs in Jerusalem

By Dawit Giorgis The most dangerous crisis in Africa is one unfolding in the Horn of Africa, in Ethiopia. It is a complicated crisis triggered by extremist elements to create an ethnocentric government, which makes one ethnic group superior to all others. The country has been sucked into a quagmire of unending internal wars and terrors that have taken countless  lives, and is characterized by one of the most gruesome crimes in history.  The country has become a failed state, with no  functional central government,  run by a group of ethnic warlords from the Oromia region, where the current PM has been elected.   After the collapse of the brutal regime of the Tigrai People’s Liberation Front (TPLF) by a popular uprising over four years ago, the Oromo-dominated government under Prime Minister Abiy Ahmed has endangered the very foundation of the country. The social fabric of this age-old nation is torn asunder, and the history of the land,  which is rooted in biblical  teachings, is under