Skip to main content

ፋሺስቱ ኦህዴዳዊው ስርአት

አሜሪካ - የፋሺስቱ ኦህዴዳዊው አፓርታይዳዊው ስርአት - የከረፋ ወንጀሉን መደበቂያና የህዝብን ድጋፍ መዝረፊያ ፈፅሞ አትሆንም! በወንድወሰን ተክሉ

አሜሪካንን ፀረ ኢትዮጲያ የሚያደርግ ክስተትም ሆነ ፀረ አሜሪካዊ ኃይል በዛሬይቱ ኢትዮጲያ አለ?

በኢትዮጲያነት ስሜት የተሰራው የእስከዛሬው ወንጀል ስቃይና መከራ ከእንግዲህ ላይቀጥል መበጣጠስ ያለበት አሁን ዛሬ ነው:: ፋሺስቱ የአቢይ መራሹ አፓርታይዳዊ ስርአት ከጀሌዎቹ ኢዜማ ጋር በመሆን አሜሪካ ኢትዮጲያን እንደሊቢያ ልታደርግ የተነሳች ቀንደኛ ጭራቅ ናት በማለት የህዝብን attention እና ድጋፍ mobilize ለማድረግ ሲንቀሳቀሱ ታይቷል:: መንጋውም - በተለይ በተለይ ምንም መማር ያልቻለው በስሜት ጋላቢ መንጋ ይህንን መንግስት መር ፕሮፖጋንዳን በማስተጋባት ፈጥኖ ሲሰለፍ ታይቷል::

የግራፊክ ምስሉ ጸሃፊውን አይወክልም!


በእርግጥ አሜሪካ ኢትዮጲያን የመበትን አላማ እቅድና ፍላጎት አላትን ? ካላትስ ለምን እና እንዴት  ብሎ ከመጠየቅ የተወረወረለትን አጥንት ለቀም አድርጎ እንደሚሮጥ ውሻ እነዚህ መሰሪዎች የወረወሩለትን የሴራና የፈጠራ ወሬን ብድግ አድርገው ሲያራግቡ ይታያል:: ተመልከቱ ይህ ለብልፅግና መንግስት እነ XYZ የፖለቲካ ኃይሎች ይመቱ በሽብርተኝነት ይፈረጁ ሚዲያዎች ይዘጉ እያለ ጥናት በማቅረብ የኢትዮጲያን ሀገረ ዴሞክራሲን ግንባታን በማደናቀፍ ቀንደኛ ጨፍጫፊ ፋሺስት ስርአትን እየፈጠረ ያለው የኢዜማው ስብስብ ሀገር ወዳድ መስሎ እና እራሱን ለሀገር ተቆርቋሪ አድርጎ አሜሪካንን እየጠራ ሲፎክር አይታችሁ እንኳን መረዳት አትችሉምን?

የኢትዮጲያን ህልውና አደጋ ላይ የጣለው የአሜሪካ ተፅእኖ ሳይሆን የአቢይና ኢዜማ ፋሺስታዊ አምባገነንነት ሆኖ ሳለ ዛሬ እነዚሁ ስብስቦች ሀገር በአሜሪካ ጣልቃ ገብነት ልትፈርስ ነው ብሎ ሲያራግቡ እንዴት ነው በጭፍን ተቀብለን ልናስተጋባ የምንችለው? 

በግብፅና በሱዳን ተጠቅመው ተጠቅመው የፈለጉትን ታርጌት አላመታ ሲላቸው ሌላ ውጪያዊ ጠላት የሚደረግ ኃይለኛ ኃይል ፈለጉና ሰሞኑን በምርጫ ጉዳይ በትግራይ ጉዳይና በሀገሪቱ ውስጥ ባለው የሰብአዊ መብት አያይዝ ላይ ጠንከር ያለ አቋም ያንፀባረቀችውን አሜሪካንን ስም ብድግ በማድረግ ሀገሬ በአሜሪካን ጣልቃ ገብነት እንደሊቢያ አትሆንም ብሎ ማናፋት የህዝባችንን ንቃተ ግንዛቤን ከመናቅና የራሳቸውንም desperate የሆነን ድድብና የወለደው ጭንቀታቸውን ከማሳየት የዘለለ አንዳችም እውነታ አያሳይም

የአሜሪካ በኢትዮጲያ ላይ የከፈተችው ዲፕሎማሲያዊ ተጽእኖ መንስኤ ምንድነው? 

ሲጀመር አሜሪካንን ልክ የአጣዬንና የመተከልን አማራዊ መንደሮችን በጭካኔ ድምጥማጣቸውን እንዳጠፋው አቢይ መራሹ ሸኔ አይን አይቶ ሀገራችንን እንደሊቢያ ልታፈራርስ ነው ብሎ የጅል ሀሳብ ማሰብን ማቆም ተገቢ ነው፡፡

አሜሪካ የምታፈርስህም ሆነ የምትገነባህ ከሆነ ስለምትጠላህና ስለምትወድህ ሳይሆን በአንተ መፈራረስና በአንተ መገንባት የምታገኘውን ጥቅሟን ለማስጠበቅ ብላ የምታደርገው መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል፡፡ የአሜሪካን የውጪ ፖሊሲ እሚፈልቀው ከወዳጅነትና ከጠላትነት እሳቤ ሳይሆን ከአሜሪካን ጥቅም ኩሬ ውስጥ የሚቀዳ ፖሊሲ ያላት ሀገር ናት፡፡

በምስራቃዊው የአፍሪካ ቀንድ ባለ 117ሚ ህዝብ ባለቤት የሆነችውን ኢትዮጲያ ሀገራዊ ህልውና እና የተዋሃደች አንድ ሉአሏዊ ሀገርነቷ ይልቅ የፈራረሰችና የተበታተነች ኢትዮጲያ የአሜሪካን ጥቅም የሚከበርባት ናት ብሎ የሚያስብ ሰው ካለ ይህ ሰው አንድ ጅሉ ሞሞ ቂሎ ወይም ሞሮን አሊያም በአሜሪካን ማስፈራሪያነት ለመነገድ ያሰፈሰፈ አጭበርባሪ ሴረኛ ሰው ብቻ ሆኖ እናያለን፡፡

ዛሬ አቢይ መራሹ መንግስትና አሜሪካ በጥሩ ሁኔታ ላይ ያለመሆናቸው ጉዳይ እውነት ነው፡፡ የተጽእኖ መንስኤ -ማለትም አሜሪካንን በኢትዮጲያ ጉዳይ አሳስቦ ጣልቃ እንድትገባ ያደረጓት አስገዳጅ ነጥቦች 

1ኛ) በኢትዮጲያ ላይ የተጋረጠው የመፍረስ አደጋ 

2ኛ) ቀጠሮ የተያዘለት የምርጫው ጉዳይ

3ኛ) የትግራይ ጉዳይ ማለትም፦

  • በትግራይ ያለው የሻእቢያ ሰራዊት ጉዳይ

  • በትግራይ ያለው ርሃብና ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ረጋጣ ጉዳይ

  • በአማራ ልዩ ኃይል ጉዳይ

  • በትግራይ እየተካሄደ ስላለው የሽምቅ ውጊያ 

4ኛ) በአማራ በኦሮሚያ በቤኒሻንጉል ስለተፈጸመው ጭፍጨፋ ጉዳይ

5ኛ) በሱዳን እና ኢትዮጲያ እና በግድቡ ጉዳይ ላይ የአሜሪካን ስጋት ተንጸባርቋል፡፡

ከዚህ ውስጥ ስሰአማራ ልዩ ኃይል ጉዳይ ማለትም የአማራ ልዩ ኃይል ከወልቃይት ጠገዴ ራያ ይውጣ ከሚለው ስህተቷ በስተቀር ያቀረበቻቸው ስጓቶቿ በሙሉ ሁላችንም የምንጋራውና እያሳሰቡን ያሉ ሀገራዊ አደጋዎች መሆናቸው ግልጽና እውነት ነው፡

በዚህም መሰረት አሜሪካ ለሀገራችን አስባ ተጨንቃና ተቆርቁራ ሳይሆን ለራሷ ጥቅም ብላ የ117ሚ ህዝብ ሀገር የሆነችው ኢትዮጲያ መፍረስ የራሷን ጥቅም የሚጎዳ መሆኑን በመሆኑ ይህንን ሀገራዊ መፍረስን አደጋ ለማስቆምና ለማስቀረት ያግዛል ብላ የነደፈችውን ፕሮፖዛል ለአቢይ በማቅረብ እንዲተገብረው ተጽእኖ እያደረገች ያለች ሆኖ ሳለ እነቆርጦ ቀጥል ብልዜማዎች -ብልጽግና እና ኢዜማ ተብዬዎች ግን አሜሪካን ኢትዮጲያን ልክ እንደሊቢያ ለማፈራረስ እንደተነሳች አድርገው ሲያስተጋቡ ለመስማት ነው የተቻለው፡፡

ይህንን የአሜሪካንን ተጽእኖን እኛ የአማራ ልጆች በጥልቀት በጥንቃቄ በመከታተል ከምናደርገው የህልውና ትግል አኳያ ለትግላችን ለህዝባችን የሚጠቅም አቋምን በተናጥል መያዝ ይገባናል እንጂ እንደግሪሳ መንጋ ሀገር ተደፈረች በሚል ማጭበርበሪያዊ ጩህት ታውረን መንጋውን መቀላቀል ፈጽሞ አይገባንም-አይጠበቅብንምም፡፡

የእኛን የአማራን ህዝብ የህልውና ትግልና አማራዊ ጥቅምን ሊጻረር የሚችለው አንድ ነጥብ ብቻ ሲሆን ያም የጀግኖቻችን የአማራ ልዩ ኃይል ከግዛታችን ወልቃይት ጠገዴ ሁመራና ራያ ይውጣ የሚለው ያልተጠና አባባል በስተቀር በአሜሪካ በኩል የተንጸባረቁት ስጋቶች በሙሉ ለትግላችን ደጀን ሆኖ የሚደገፈን እንጂ የሚጊጎዳን ፈጽሞ አይደለም፡፡

የተመለሱ ግዛቶቻችንን በተመለክተ እያንዳንዱ አማራ ማወቅ ያለበት መመሪያ ግዛታችንን የሚያስጠብቀው አቢይም ሆነ ሌላ ኃይል ሳይሆን የእኛው የአማራ ህዝብ ብቻና ብቻ መሆኑን ማወቁ ላይ ነው፡፡

መሬታችንን ህወሃት ከሰላሳ አመት በፊት የወሰደችው አማራ ብልተደራጀበት በጉልበቷና በኃይል ሲሆን ዛሬም በእጃችን ያስገባነውን ግዛታችንን የሚነጥቀን የአሜሪካን ትእዛዝዛ የአቢይ ሴራ ሳይሆን የእኛ የአማራ ልጆች ተጠናክሮ ተደራጅቶ መገኘት ብቻ ነው፡፡

እናም የአማራው የህልውና ትግል የአሜሪካንን ወዳጃነትና ድጋፍፍን ይፈልጋል እንጂ ለፋሺስቱ አቢይና ኢዜማ ጥቅምና  ስልጣን ብሎ  አሜሪካንን እያወገዘ ጠላት የሚፈጥርበት ሁኔታ ላይ አይደለንም፡፡


Comments

Popular posts from this blog

ዐማራን ወክሎ ከወያኔ ጋር ስለሰላምም ሆነ ስለትጥቅ ትግል አልፎም ስለመንግሥት መሥረታ መነጋገር ፈጽሞ አይቻልም

ዐማራን ወክሎ ከወያኔ ጋር ስለሰላምም ሆነ ስለትጥቅ ትግል አልፎም ስለመንግሥት መሥረታ መነጋገር ፈጽሞ አይቻልም፤ ዐማራ የተጨፈጨፈው በሦስት ዓመት ዕድሜ ውስጥ ብቻ አይደለም። በ17 ዓመት የወያኔ የሽፍተነት ዘመን፣ 27 ዓመት የወያኔ የመንግሥትነት ዘመን ወደኋላ ተጨምሮ ነው። ከውያኔ ጋር ሰላምን ወይም ትጥቅ ትግልን እናደርጋለን የሚሉ ሁሉ ውሾች ናቸው። "ውሻ ወደ ትፋቱ ይመለሳል" በምሣሌ 26፤11 እና 2ኛ ጴጥሮስ2፤22 የተጠቀሰውን መጽሐፋዊ ዘገባ በማንበብ ከውያኔ ጋር የመከሩትን የውሾች ባህሪ ለይቶ መረዳት ነው። ምስሉ ጸሃፊውን አይወክልም 1ኛ. የዐማራን ሕዝብ የመደብ ጠላት አድርጎ ወያኔን በደደቢት የመሠረተውና 17 ዓመት በትጥቅ ትግል 27 ዓመት በመንግሥትነት በደምሩ 44 ዓመት ከሰባት ሚሊዮን በላይ ዐማራን ሕዝብ ያለማቋረጥ ያስጨፈጨፈ፣ ርስቱን የነጠቀ በጀምላ የገደለ ያፈናቀለ፣ የትግራይን ሕዝብ ከኢትዮጵያዊ ቀዳሚ ሕዝብነቱና ማንነቱ ያስከዳ ስብሐት ነጋ ፤   2ኛ. ከዐማራ ሕዝብ ይልቅ የሱዳን ሕዝብ ይሻለናል ብሎ በማይካድራ በጭና ዐማራን በከፍተኛ መራር በሆነ ጭካኔ ያስጨፈጨፈው፣ በመጨረሻ ተረጋግቶ መኖር ሲችል ዕቅድና ዓላማ በሌለው ጦርነት አንድ ሚሊዮን የትግራይ ወጣት ያስጨፈጨፈ፣ የትግራይን ሕዝብም ሆነ የዐማራን ሕዝብ አዘቅት ውስጥ የከተተ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ፤   3ኛ. የወያኔ ተሿሚ ሆኖ የዐማራን መሬት ፀገዴና ጠገዴ እያለ እየከፋፈለ ለወያኔ ያስረከበ፣ የግጨውን መሬት ለወያኔ በችሮታ ፈርሞ የሰጠ፤ እነ ዶክተር አባቸው ለማስገደል ቅድመ ሁኔታዎችን ከአመቻቸ በኋላ ወደ አሜሪካ ሀገር ሾልኮ ወጥቶ ከተገደሉ በኋላ ተመልሶ ጥቁር ለብሶ የዓዞ እንባ ሲያነባ ሲመጻደቅ የነበረ የሕወሀትም ሆነ የብልጽግና ቀንደኛና ፊ...

በጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay)

ሻለቃ ዳዊትን በተለያዩ ምክንያቶችና ወቅቶች እንደ እኔ የተቻቸው ፈልጋችሁ አታገኙም። ያ ወቅት ሌላ ፤ ዛሬ ሌላ፤- ያ ዘመን ከ2010 ዓ.ም በፊት ነው። ሰው የነበረውን መስመር አስተካክሎ ባዲስ አካሄድ ወቅቱ በሚጠይቀው ጎዳና ከተራመደ ሌላ ምን ይፈለጋል? ዛሬ ግን ሻለቃው “ኢምፖስተር” በማለት የሚጠሩት ህቡእና ግልጽ ነብሰገዳይ ቡድን አሰማርቶ ነብስን የሚቀጭና የሚሰውር <<የወያኔ የነገድ አስተዳዳር አስቀጣዩ የኦሮሙማው የጋጠወጥ ማፍያዎች መሪ>> አብይ አሕመድ ከነገሠ ወዲህ ግን “ሻለቃው” አብይ አሕመድን እንቅልፍ ካሳጡት አርበኞች አንዱ ሆነው ብቅ ብለዋል። ያንን በማድረጋቸው “ጥበብ ሳሙኤል” የተባለ የአብይ አሕመድ አለቅላቂና ፀረ አማራና የሕግ ሙያ ትምሕርተ አለበት ተብሎ የሚነገርለት (?) ጋዜጠኛ:- አብይ አሕመድን በመደገፍ በሻለቃው ላይ ያለ ዕረፍት ረዢም ጊዜ ሲዘልፋቸው ያስገረመኝ ያህል፤ ሰሞኑን ደግሞ በሻለቃ ዳዊት ወ/ልደጊዮርጊስ ላይ አዳዲስ ዘላፊዎች ብቅ ብለዋል። “ሻለቃ ሆይ! በትግሉ ውስጥ ዛሬ ይኑሩ አይኑሩ አማራውን ለመታደግ ከፍታዎትን አሳይተዋል ፤የበኩልዎን አድርገዋል ለዚህም <<በአክብሮት ባርኔጣየን አነሳለዎታለሁ፤ አንኳን ደስ አለዎት !!!!>> አርበኛ ብቅ ባለ ቁጥር ሱሪውን የሚጎትቱ ብዙ የፖለቲካ ተውሳኮች አሉ። ሻለቃው በዛው ዕደሜአቸው የሚቻላቸውን በማድረጋቸውና ከፍታቸውን በማሳየታቸው ፤ ይህን በማድረጋቸው ዓይናቸው ከቀላ ውስጥ አንዱ ወደ “ጥንት ትፋቱ” የተመለሰው፤ በቅርቡ ከወያኔም ከኦነጎችም እየተወዳደሰ መተፋፋግ የጀመረው የወያኔው አሽከር “ኤርሚያስ ለገሰ” እና ዶ/ር አምሳሉ የተባለ “ከጎንደሬዎች እጅህን አንሳ” እያለ ሲከራከረኝ የነበረው እስከ ቅርብ ጊዜ ወዲህ የአብይ አሕመድ አወዳሽ የነበ...

Creeping Genocide: in Ethiopia by Dawit W Giorgis

“The number of dead and buried based on latest information for human rights activist on the spot: 1511 dead already collected and buried 300 more discovered not yet buried and more than 10000 fleeing.” Dawit W Giorgis By Dawit W Giorgis (This article is available in Amharic, French and German) As I write this article AP on June 20 reports: “Witnesses in Ethiopia said Sunday (June 19) that more than 200 people, mostly ethnic Amhara have been killed in an attack in the country’s Oromia region.” A source from inside Ethiopia informs me: 400 Amharas were killed and 6000 are in hiding. “Another source quoted an elderly Muslim Amhara man; “We ran to hide in the mosque. They entered the mosque and killed 46 people and 12 of my family members. I wished that they had killed me too. Why did Alah spare me? I would have liked to die with them.” Witnesses state children as young as 5 were slaughtered like animals in public. These are the grim realities in Ethiopia in the last four years.” The last ...