Skip to main content

ሻ/ቃ ዳዊት ወ/ጊወርጊስ ስለራሳቸው የጻፉት ።ከታች ያለውን የሻለቃ ዳዊት ወ/ጊዎርጊስን የግል ፅሁፍ እንመልከት ።

ሻ/ቃ ዳዊት ወ/ጊወርጊስ ስለራሳቸው የጻፉት ። 

Dawit W/Giorgis


የአማራ ሕዝባዊ ግንባር የውጭ ድጋፍ ሰጪ ግብረ ሀይልን እዚህ ለማድረስ ቁልፍ ሚና በመጫወቴ ደስተኝ ነኝ:: ይህንን እድል ለሰጠኝ ወደር ለሌለው ጀግና እስክንድር ነጋ ምስጋናዬን እቀርባልሁ:: ይህንን  ግዙፍ ሀላፊነት  ለመወጣት ከሚታወቀው  በላይ ያለ እረፍት ሌት  ተቀን  የሰሩትን የስራ ባልደረቦቼን እደንቃለሁ:: አመሰግናለሁ:: 

እኔ የስራ ሰው ነኝ:: የእወቀትም ሰው ነኝ:: ታሪካዊና ትምህርታዊ  የሆኑ አራት  መፅሀፎችም ፅፌአለሁ:: በእንግሊዝኛም በአማርኛም::አልቀረብኝም:: ቁጥራቸው በጣም ብዙ የሆኑ ምሁራዊ  ፅሁፎችን አሳትሜአለሁ::ከአውስትራሊያ አውሮፓና አሚሪካ ካናዳ የተለያዩ ሚዲያዎች ላይ  ለብዙ አመታት ቀርቤአለሁ:: ፅሁፎቼም በ CNN ሳይቀር ወጥተውልኛል:: 

አገልግሎቴን ግን የምመዝነው በተግባሬ ነው:: እውቀቴን  በተግባር   በማዋል የተመሰከረልኝ  ነኝ:: እውቀትና ተግባርን በማያያዝ በውትድርና ሙያ፣ በኤርትራ  አስተዳዳሪነት፣ በዲፕሎማሲ፣ በተባበሩት መንግስታትና ለተለያዪ መንግስታት በችሎታ አማካሪ ሆኜ  አገልግያለሁ:: 

ሰውም የሚያውቀኝ : እኔም እራሴን የማውቀው እንደ  ተግባር  ሰው ነው::እውቀቴን ለተግባሬ መሳሪያ እድርጌ የኖርኩ ከጦርሜዳ እስክ ህይወት  ማዳን ታላላቅ  ዘመቻዎች (humanitarian operations) በእውቀትና በኩራት ያገለግልኩ ነኝ:: ለኢትዮጵያ  አንድነትና ለአገሬ ህዝብ ፍቅሬን በደሜ አስመክሬአለሁ::

በውጊያ ቆስያለሁ:: አድር ባይ ሆኜ  በደርግ የፖለቲካ ሥርዓት መቆየት ስችል  ከሥርዓቱ መራቅ ብቻ ሳይሆን ወጥቼ  ስርአቱን ለማስለወጥ  ረዥምና ውስብስብ ትግል ውስጥ የነበርኩ ነኝ:: ለዚሁ ትግል በሱዳንና በኬንያ ጠረፎች አድርገን  አንዳንድ ሁኔታዎችን ለማስተባበር  አገር ቤት በድብቅ  በእግር ገብቻለሁ:: በጊዜው እድሜዬም ትንሽ አልነበረም:: 

ደርግ ስሜን ለማጥፋት ያደረገውን  ዘመቻ በህግ ሀሰት መሆኑን እስመስክሬአለሁ::

በአንድ ህይወት ይህንን ያህል የሥራ ውጤት ያካበተ ብዙም ሰው አይገኝምብል ማጋነን አይሆንብኝም። ለዚህም እግዚአብሄርን ከማመስገን  አላቋርጥም::ለእዚህ ነው የመጨረሻውን  መፅሀፌን “What a Life” ያልኩት:: ብዙ ድካምና  ጊዜ የወሰደ መፅሀፍ ነው::  የሶስቱም መፅሀፎች ሽያጭ  ለበጎ ስራ የተሰጡ ናቸው:: ማሳተሚያውን በግሌ ነው የከፈልኩት:: የመጨረሻው ግን በአስተዋፅኦ ነው የተከፈለው:: 

አማራ ሲጎዳ፣  የዘር ማጥፋት ወንጀል ሲፈፅምበት ከጎኑ ቆሜአለሁኝ:: አብይንና የወንጀሉ እስፈፃሚዎችን በኢንተርናሽናል ፍርድ ቤት ለማቅረብ  ሌሎች ስራዎቼን እቁሜ ለሁለት አመት በጎደኞቼ ድጋፍ ጥናቱን አጠናቀን ለፍርድ ቤት አቅርበናል::  የኢንተርናሽናል ፖለቲካ መሰናክል እጋጥሞን አብይ አህመድ ፍርድ ቤት ገና አልቀረበም::  ከዚያም በሁዋላ ብዙ ወንጀሎች ስለ ተፈፅሙ  ተጭማሪ ስራዋች ይጠይቃል::  በጊዜው  ከነበረችው የፍርድ ቤቱ አቃቤ ሕግ ( ICC prosecutor general) ጋር ለዚህ ጉዳይ በቀጥታ የተገናኘ ሌላ ኢትዮጵያዊ አላውቅም:: ከእኔ ጋር በቀጥታ ተፃፅፈናል:: በእሷ ሥር ከነበሩ የህግ አዋቂዋችና የክፍል ሃላፊዋች  ጋር ክሱን በተመለከተ  ፕሮፌሽናል ውይይት እድርገናል:: ጥናቱም ሆነ ለዚህ ጥረት ተብሎ የተሰበሰበው ገንዘብ በቤተ ክህነቱ አካውንት ይገኛል:: 

ዛሬም ከእስክንድር ሌላ ጥሪ ሲመጣብኝ ስራዬን ሙሉ ለሙሉ አቁሜ ተቀላቅየዋለሁኝ:: ራሴን ጡረታ ካስወጣሁ በሁዋላ The Africa Institute for Strategic and Security Studies (AISSS) www. aisss.org አፍሪካ ምድር አቋቁሜ  የድርጅቱ ዋና ስራ እስኪያጅ  ሆኜ በመስራት ያለሁበትን ትቼ  አለክፍያ ሙሉ ለሙሉ ጊዜዬን  ለፋኖ ትግል ስጥቻለሁ:: የፋኖ እንቅስቃሴ  ከተጀመረ  በሁዋላ በአለም ደረጃ   ትግላችን እንዲታወቅ የተደረገው  ከግንባሩ ምስረታ በሁዋላ ነው::በኢንትርሽናል ደረጃ  በአውሮፖና  በአሜሪካ በአፍሪካ ( በዲፕሎማሲ ዘርፍ) በይፋ ከተነገሩት  ሌላ በግንባሩ ስም እኔ የፈፅምኳቸው ጊዜው ሲደርስ  ይገለፃሉ:: 

በአስራ ስባት አመቴ  ወታደርነት የታጨሁ: ሶስት አመት ከታወቀው የቀኃስ  ወታደራዊ  አካዳሚ የሰለጠንኩ: አንድ አመት አሜሪካን አገር 10 ወር  ሌላም ቦታ ለጥቂት ወራት  ተጨማሪ ልዩ  ስልጠና የፈፅምኩ ኩሩ ወታደር ነኝ::  አራት አመት ቀኃስ ዪኒቨርስቲ: (LLB)   ከዚያ ሁለት ዓመት ኮሎምቢያ ዩኒቨርስቲ ( JD – Doctor of Jurisprudence)  ቀጥሎ  SMU ቴክሳስ ለPhD ቆይቼ  የእናት አገር ጥሪን ተቀብዬ በደርግ ጊዜ አገሬ ተመልሻለሁ::ከዚህም በላይ በሶስት ታላላቅ ዩኒቨርሲቲዋች ( Princeton, Universty of Cape Town,Boston University, African Studies Center) በተለያዩ ጊዚያት Visting Scholar ሆኜ ተስይሜ ምርምር ስራዎች ውስጥ ተሳትፌአለሁኝ:: 

እንደ ዛሬው ሳይሆን በቀድሞ አባቶቻችን አርበኝነት ስሜትና ሥነስርአት ተኮትኩቼ እዚህ የደረስኩ: የዘመኑ ትምህርትና ምቾት ያልለወጠኝ ኩሩ ልበ ሙሉ ኢትዯጵያዊ ነኝ::  የእኔ አማራነት፣ የእኔ እስተዋፅኦ፣ የእኔ ኢትዮጵያዊነት በጥቂት የሴራ ፓለቲከኞች፣ ቡድንተኞችና ምቀኞች  የሚተች አይደለም:: በጠባብ እውቀት: እዚህ ግባ በማይባል ልምድ: ወይንም አለምንም ልምድ: ድንበር  በዘለለ ምቀኝነት: የእኔን ምንነትና ማንነት ማንቋሸሽ ጊዜው እልፎአል:: ህይወቴ ሲፈተሽ ኖሮአል::  ምክትል ሚኒስትር፣ በሚኒስትር ደረጃ ኮሚሽነር፣ የኤርትራ ክፍለሀገር ዋና ተጠሪ የነበርኩ፤ ከሁለተኛው ዓለም ጦርነት በሁዋላ  ያልታየ  ታላቅ ኢንተርናሽናል የረሀብ ዘመቻ  የመራሁ፣ በብዙ  አለም አቀፍ ፅሁፎችና መድረኮች  የተጠቀስኩ፣ ከብዙ መንግስታት መሪዋች ጋር  በልኡካን መሪነት ቀጥሎም ከ25 ዓመት  በላይ በኢንተርናሽናል አማካሪነት አፍሪካ የስራሁ፣ ለመሪዎች ጥናት ያቀረብኩ፣  ከታላላቅ  ስዎች ጋር የተወያየሁ፣  ብዙ የተመስገንኩና የተከበርኩ  ሰው ነኝ:: 

አማራን ለማደራጀትና  ማህበራቱ በአንድ  ጃንጥላ  ስር  ሆነው እንዲታገሉ የዛሬ ስምንት  ዓመትና ከዚያም በሁዋላ ከቅርብ የትግል ወዳጆቼ  ጋር  ( አቶ ሃይለ ገብርኤል እስረስና ፕሮፌስር ጌታቸው በጋሻው) ብዙ  እልህ አስጨራሽ  ስብስባዎች መርቻለሁ:: በመጨረሻም “አንድ አማራ” የሚለውን ድርጅት አዋልደናል:: አብይ ስልጣን ላይ ሲወጣ  ድርጅቱ  ከሰመ:: አሁን ያለው “አንድ አማራ” ከቀድሞው ጋር የተያያዘ አይደለም::

Comments

Popular posts from this blog

የጋራ ጠላታችንን ልናሸንፈው የምንችለው ብአንድነት ብቻ ነው:: ሻ/ቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ

ከዚህ መከፋፈል ነፃ ሆነን ፊትለፊት  እየወረረ : እየገደለን: ያለውን የጋራ ጠላታችንን ልናሸንፈው የምንችለው ብአንድነት ብቻ ነው:: ሻ/ቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ ሻ/ቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ በምናየው  ታላቅ  የፋኖ ትግል የዲያስፓራ ትልቁ ስራ ገንዘብ መስብስብ ነው:: እሱም እየቀዘቀዘ ሄዷል:: ጦርነቱን ያራዝምነው እኛው ነን:: ይህ ደግሞ ትልቁና ዋናው የጠላት ስትራተጂ ነው:: ጦርነቱን ማራዘምና ከአማራ ምድር እንዳይወጣ በማድረግ: ፋኖን በመከፋፈል አዳክመዋለሁ ! እበትነዋለሁ ! የሚል የአቢይ አህመድ ትልቁ  የወቅቱ ስትራተጂ መሆኑን ተረድተናል::: በዚህም ምክንያት በአጠረ ጊዜ  ሊጠናቀቅ የሚችለውን  ትግል  ዲያስፓራ በምቀኝነት: በቅናት: በሌለ  ስልጣን  ላይ በመፋተግ: በተቀጣሪነት: በጠባብ አስተሳስብ: ትግላችንን ወደኋላ  በመጎተትና  እንዲራዘም ብሎም እንዲዳከም በማድረግ ታሪካዊ ወንጀል እየስራ ነው:: ከዚህ መከፋፈል ነፃ ሆነን ፊትለፊት  እየወረረ : እየገደለን: ያለውን የጋራ ጠላታችንን ልናሸንፈው የምንችለው በአንድነት ብቻ ነው::  አሸናፊነት ትብብርና  የጋራ ስትራተጂ ይጠይቃል:: የተግባር ዲያስፓራ እንሁን:: አማራን እንደ  ህዝብ ኢትዮጵያንም እንደ ሀገር  ለማዳን  ዋናው መሳሪያችን  አንድነት ነው:: በውስጣችን ያለውን ልዩነት በመጠቀም  አገራችንን ለማጥፋት: በአካባቢያችን  ያለውን የሀይል አሰላለፍ ስንመለከት ፍፁም ፍፁም  አደገኛ  መሆኑን እንገነዘባለን:: በዲያስፓራ  መጨቃጨቅና መዘላለፍ  እንደ ባህልና እንደ ትልቅ   የጦርነት ስትራተጂ ተደር...

ዐማራን ወክሎ ከወያኔ ጋር ስለሰላምም ሆነ ስለትጥቅ ትግል አልፎም ስለመንግሥት መሥረታ መነጋገር ፈጽሞ አይቻልም

ዐማራን ወክሎ ከወያኔ ጋር ስለሰላምም ሆነ ስለትጥቅ ትግል አልፎም ስለመንግሥት መሥረታ መነጋገር ፈጽሞ አይቻልም፤ ዐማራ የተጨፈጨፈው በሦስት ዓመት ዕድሜ ውስጥ ብቻ አይደለም። በ17 ዓመት የወያኔ የሽፍተነት ዘመን፣ 27 ዓመት የወያኔ የመንግሥትነት ዘመን ወደኋላ ተጨምሮ ነው። ከውያኔ ጋር ሰላምን ወይም ትጥቅ ትግልን እናደርጋለን የሚሉ ሁሉ ውሾች ናቸው። "ውሻ ወደ ትፋቱ ይመለሳል" በምሣሌ 26፤11 እና 2ኛ ጴጥሮስ2፤22 የተጠቀሰውን መጽሐፋዊ ዘገባ በማንበብ ከውያኔ ጋር የመከሩትን የውሾች ባህሪ ለይቶ መረዳት ነው። ምስሉ ጸሃፊውን አይወክልም 1ኛ. የዐማራን ሕዝብ የመደብ ጠላት አድርጎ ወያኔን በደደቢት የመሠረተውና 17 ዓመት በትጥቅ ትግል 27 ዓመት በመንግሥትነት በደምሩ 44 ዓመት ከሰባት ሚሊዮን በላይ ዐማራን ሕዝብ ያለማቋረጥ ያስጨፈጨፈ፣ ርስቱን የነጠቀ በጀምላ የገደለ ያፈናቀለ፣ የትግራይን ሕዝብ ከኢትዮጵያዊ ቀዳሚ ሕዝብነቱና ማንነቱ ያስከዳ ስብሐት ነጋ ፤   2ኛ. ከዐማራ ሕዝብ ይልቅ የሱዳን ሕዝብ ይሻለናል ብሎ በማይካድራ በጭና ዐማራን በከፍተኛ መራር በሆነ ጭካኔ ያስጨፈጨፈው፣ በመጨረሻ ተረጋግቶ መኖር ሲችል ዕቅድና ዓላማ በሌለው ጦርነት አንድ ሚሊዮን የትግራይ ወጣት ያስጨፈጨፈ፣ የትግራይን ሕዝብም ሆነ የዐማራን ሕዝብ አዘቅት ውስጥ የከተተ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ፤   3ኛ. የወያኔ ተሿሚ ሆኖ የዐማራን መሬት ፀገዴና ጠገዴ እያለ እየከፋፈለ ለወያኔ ያስረከበ፣ የግጨውን መሬት ለወያኔ በችሮታ ፈርሞ የሰጠ፤ እነ ዶክተር አባቸው ለማስገደል ቅድመ ሁኔታዎችን ከአመቻቸ በኋላ ወደ አሜሪካ ሀገር ሾልኮ ወጥቶ ከተገደሉ በኋላ ተመልሶ ጥቁር ለብሶ የዓዞ እንባ ሲያነባ ሲመጻደቅ የነበረ የሕወሀትም ሆነ የብልጽግና ቀንደኛና ፊ...

በጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay)

ሻለቃ ዳዊትን በተለያዩ ምክንያቶችና ወቅቶች እንደ እኔ የተቻቸው ፈልጋችሁ አታገኙም። ያ ወቅት ሌላ ፤ ዛሬ ሌላ፤- ያ ዘመን ከ2010 ዓ.ም በፊት ነው። ሰው የነበረውን መስመር አስተካክሎ ባዲስ አካሄድ ወቅቱ በሚጠይቀው ጎዳና ከተራመደ ሌላ ምን ይፈለጋል? ዛሬ ግን ሻለቃው “ኢምፖስተር” በማለት የሚጠሩት ህቡእና ግልጽ ነብሰገዳይ ቡድን አሰማርቶ ነብስን የሚቀጭና የሚሰውር <<የወያኔ የነገድ አስተዳዳር አስቀጣዩ የኦሮሙማው የጋጠወጥ ማፍያዎች መሪ>> አብይ አሕመድ ከነገሠ ወዲህ ግን “ሻለቃው” አብይ አሕመድን እንቅልፍ ካሳጡት አርበኞች አንዱ ሆነው ብቅ ብለዋል። ያንን በማድረጋቸው “ጥበብ ሳሙኤል” የተባለ የአብይ አሕመድ አለቅላቂና ፀረ አማራና የሕግ ሙያ ትምሕርተ አለበት ተብሎ የሚነገርለት (?) ጋዜጠኛ:- አብይ አሕመድን በመደገፍ በሻለቃው ላይ ያለ ዕረፍት ረዢም ጊዜ ሲዘልፋቸው ያስገረመኝ ያህል፤ ሰሞኑን ደግሞ በሻለቃ ዳዊት ወ/ልደጊዮርጊስ ላይ አዳዲስ ዘላፊዎች ብቅ ብለዋል። “ሻለቃ ሆይ! በትግሉ ውስጥ ዛሬ ይኑሩ አይኑሩ አማራውን ለመታደግ ከፍታዎትን አሳይተዋል ፤የበኩልዎን አድርገዋል ለዚህም <<በአክብሮት ባርኔጣየን አነሳለዎታለሁ፤ አንኳን ደስ አለዎት !!!!>> አርበኛ ብቅ ባለ ቁጥር ሱሪውን የሚጎትቱ ብዙ የፖለቲካ ተውሳኮች አሉ። ሻለቃው በዛው ዕደሜአቸው የሚቻላቸውን በማድረጋቸውና ከፍታቸውን በማሳየታቸው ፤ ይህን በማድረጋቸው ዓይናቸው ከቀላ ውስጥ አንዱ ወደ “ጥንት ትፋቱ” የተመለሰው፤ በቅርቡ ከወያኔም ከኦነጎችም እየተወዳደሰ መተፋፋግ የጀመረው የወያኔው አሽከር “ኤርሚያስ ለገሰ” እና ዶ/ር አምሳሉ የተባለ “ከጎንደሬዎች እጅህን አንሳ” እያለ ሲከራከረኝ የነበረው እስከ ቅርብ ጊዜ ወዲህ የአብይ አሕመድ አወዳሽ የነበ...