Skip to main content

ከኢትዮጵያ መፍረስ በኋላ የአማራ ህልውና እንዴት ይቀጥል⁉ (ለማይቀረው የአባት ሀገር አማራ ምስረታ እንዘጋጅ ‼)


በዴቭ ዳዊት

ከኢትዮጵያ መፍረስ በኋላ የአማራ ህልውና እንዴት ይቀጥል⁉

(ለማይቀረው የአባት ሀገር አማራ ምስረታ እንዘጋጅ ‼) 

/ክፍል-1/ 

=============== መግቢያ =============== 

* እኔ ዳዊት ይህንን ፅሁፍ የፃፍሁት እውነትን (no matter how it's bitter and ugly) በድፍረት መጋፈጥ ለማይፈሩ፣ ከስሜት ይልቅ ለዕውቀት የተደላደለ አዕምሮ ላላቸው፣ እንዲሁም አይቀሬ አዲስ ክስተቶችን ለመቀበል ለማይቸገሩ ይልቁንም ከ new reality  ጋር እንዴት  cope up ማድረግ እንዳለባቸው ማሰላሰል ለሚችሉ የአማራ ልጆች ነው። በመሆኑም፦ 

1. Intellectually pygmy የሆኑ፣ 

2. ከእውነት ይልቅ በቅዠት ዓለም መኖር የሚመርጡ፣ 

3. በ imperial nostalgia እየማቀቁ የሀገሪቱን pre-1991 ካርታ በየአደባባዩ ተሸክመው የሚዞሩ ግለሰቦችና ቡድኖች ይህንን ፅሁፍ እንዲያነብቡት ምኞቱም ፍላጎቱም የለኝም‼‼‼ 

=====አዝጋሚው የኢትዮጵያ መፍረስ እውን መሆን ======

* ኢትዮጵያ የመበተኗ ጉዳይ አይቀሬ ነው‼ የኢምፓየሯ መፍረስ fait accompli ከሆነ ውሎ አድሯል። የአማራ ህዝብ ሀገሪቱን በማፍረስ ረገድ አንዳችም ሚና ያልነበረውና በ Karl Jasper የ guilt መስፈርት ብንመዝነው እንኳ Criminally, Morally, Politically and Metaphysically ህዝባችንን ተጠያቂ አልያም ተፀፃች ሊያደርገው የሚችል እንጥፍጣፊ ጉዳይ አይኖርም‼ 

ይልቁንስ የአማራ ህዝብ ከዚህ በኋላ እንኳንስ በምድራዊ ኃይል ይቅርና አማልክትም እንኳ ተሰብስበው በአንዳች ተአምራዊ  panacea ቢያክሟት እንኳ ከፍርሰት ልትድን ስለማትችለው ኢትዮጵያ እርግፍ አድርጎ ትቶ የራሱን አባት ሀገር በፍጥነት ስለመመስረት ማሰብ ያለበት ትክክለኛ ወቅት ላይ እንገኛለን‼‼‼ 

ከሀገሪቱ መፍረስ እውን መሆን ውስጥ እርግጠኛ መልስ ያላገኘው ጥያቄ ቢኖር የመፍረሱ ሂደት የሚጠናቀቀው፦ 

1. In what form? እና 

2. By what time frame? የሚለው ብቻ ነው‼ 

የዚህ ፅሁፌ አላማም በተራ ቁጥር 1 ላይ በተጠቀሰው ነጥብ ዙሪያ የሚያጠነጥን ይሆናል። መልካም ንባብ! 

* ኢትዮጵያን እንደማንኛውም multiethnic and territorially integrated empire ከማየት ይልቅ በራሱ ልሂቅ ለዘመናት  "ብፅዕትና ቅድስት ከሀገራትም የተለየች ሀገር" እንደሆነች ተደርጎ ሲነገረው ለኖረ አማራዊው ህዝባችን፥ ሀገሪቱ በአይቀሬው ሞቷ አፋፍ ላይ ሆና እንኳ ይህንን እውነት ተቀብሎ ከፍርስራሹ መሐል ራሱን እንዴት ማዳን እንዳለበት፤ የራሱን ሉዓላዊ አባት ሀገር ለመመስረትም ቅድመ ዝግጅት ከማድረግ ይልቅ አስፈሪውን መፃኢ ጊዜ በድንዛዜ እጁን አጣጥፎ በመቀመጥ መጠበቁ እጅግ አስደንጋጭ ነው። 

በእርግጥ የዚህ አይነቱ collective ድንዛዜ ተራ ክስተት ሳይሆን በህዝባችን ላይ ለተራዘመ ጊዜ በተሰራበት ህፅበተ-አዕምሮ (Brain wash) ምክንያት ያፈጠጠ ስቃዩ እንዳይ'ሰማው ሆኖ ለከፍተኛ የስነልቦና ቀውስ ዳርጎታል። ይህ በህዝባችን ውስጥ  ገንግኖ ስቃይንና አደጋን አስረስቶ በማደንዘዝ ህዝባችንን ወደ ፈፅሞ መጥፋት እየነዳ የሚገኘው  የስነልቦና መቃወስ  La Belle Indifférence ("Beautiful Ignorance") ብለን ልንጠራው የምንችለው አይነት አደገኛ ድንዛዜ ነው። 

የአማራ ህዝብ በዚህ መጠን ለምን ደነዘዘ? Collectively የ  La Belle Indifférence ሰለባስ እንደምን ሆነ?  እየሞተች ካለችው ኢምፓየር ጋር አብሬ ካልጠፋሁ ብሎ የራሱን ሀገር ከመገንባት ይልቅ እጁን አጣጥፎ ለምን ተቀመጠ? ብለን ከጠየቅን መልሱ የሚሆነው የ Asymmetric Fear ሰለባ በመሆኑ ነው‼ ይህንን asymmetric fear ደግሞ more specific እናድርገው ካልንና በትክክለኛ ስሙ እንጥራው ካልን የአማራ ህዝብ እንደ ህዝብ በጋራ የ Separation Anxiety Disorder (S.A.D) ሰለባ ሆኗል‼‼‼ "ከኢትዮጵያ ተነጥዬ መኖር አልችልም፣ ኢትዮጵያ በአሁን ቅርጿና የህዝቦቿ ስብስብ ካልቀጠለች መኖር አልችልም" የሚል መሠረተ ቢስ ፍርሃት‼‼‼ 

ይህ unwarranted ፍርሃት እንዲሁ በድንገት በአንድ ሌሊት የተፈጠረ ሳይሆን፥ ከላይ ለመግለፅ እንደሞከርሁት፥ ለዘመናት በዋናነት በራሱና በሌሎች ልሂቃን ስለ ኢትዮጵያና ስለራሱ ሲነገረው በኖረ የመሰሪዎች ተረት ምክንያት ነው። ከእነዚህ የማደንዘዣ ተረቶች መካከልም የተወሰኑትን አንስቶ ማለፍ ከዚህ unwarranted fear bondage ለመላቀቅ በጥቂቱም ቢሆን ይረዳል የሚል እምነት አለኝ። 

1. "The White man's Burden" Analogy፦ የአማራን ህዝብ የስልጣን ወንበሩ ማስጠበቂያ ማድረግ የሚፈልግ ገዢ አምባገነንና በኪነጥበብ ስም የሚገለሙት አዝማሪ ሁሉ ህዝባችንን ሲሸነግለው የኖረው "አማራ የኢትዮጵያ ጠባቂ ነው፣ አማራ ከኢትዮጵያዊነት እንዴት ይወርዳል? ፣ አማራ እየተገደለም ቢሆን ከኢትዮጵያዊነት አይወርድም፣ ሀገር ማቅናት በአማራ ትከሻ ላይ ነው የወደቀው፣..........." ወዘተ በሚል ድሪቶ ተረት ተረት ነው። ተላላው ህዝባችንም ይህንን የብልጣብልጦች ተረት አምኖ 82 ብሔር በሚኖርባትና አማራ በማንነቱ ምክንያት የሚሳደድባትን ሀገር "ዋልታና ማገሯ እኔ ነኝ" ብሎ አምኖ ኖሯል። በመሆኑም በአናቱ ላይ ሀገሪቱ እየፈረሰች እያየ እንኳ ተፈጥሯዊ የሆነ ራስን የማዳንና ትውልድን የማስቀጠል እንዲሁም ማረፊያ አባት ሀገር የመመስረቱን ጉዳይ ለዘመናት ሲሰበክ ከኖረው ተረት ጋር እያመሳከረ ትልቅ ወንጀል የፈፀመ አልያም ይህንን ማሰብ በራሱ እንደ grand dereliction በመቁጠር በፍርሃት ቆፈን ተይዞ ሀገር አልባና "የአፍሪካው ጂፕሲ" ለመባል እያጣጣረ ይገኛል። 

የእኛ የአማራ ብሔርተኞች የመጀመሪያ ተልዕኳችንም ይህንን ተረት ተረት ከአማራ ህዝብ ልብና አዕምሮ ፍቆ በማስወገድ መሰሪ ገዢዎችና በኪነጥበብ ስም የሚገለሙቱ አዝማሪዎች በህዝባችን አዕምሮ ውስጥ የሳሏትን ጣዖቷን ኢምፓየር ከእሳቤው ውስጥ ሰባብረን በመጣልና ከፍርሃቱ ነፃ በማውጣት ከእውነታው ጋር በፍጥነት ታርቆ ታሪካዊ ርስቱንና ወሰኑን በማስከበር ሉዓላዊ አማራዊ አባት ሀገሩን እንዲመሠርት ማድረግ ነው‼‼‼

2. "The Chosen People" Analogy፦ 

====== ክፍል ሁለት ይቀጥላል======

* የጠራ ራዕያችን ፥ ሉዓላዊው አባት ሀገር አማራ ተመስርቶ ከጄኖሳይድ የተረፈው ህዝባችን በነፃነት ሲኖር ማየት ነው‼‼‼

ፈጣሪ የአማራን ህዝብ አብዝቶ ይባርክ‼‼‼

ዴቭ ዳዊት።

Comments

Popular posts from this blog

የጋራ ጠላታችንን ልናሸንፈው የምንችለው ብአንድነት ብቻ ነው:: ሻ/ቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ

ከዚህ መከፋፈል ነፃ ሆነን ፊትለፊት  እየወረረ : እየገደለን: ያለውን የጋራ ጠላታችንን ልናሸንፈው የምንችለው ብአንድነት ብቻ ነው:: ሻ/ቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ ሻ/ቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ በምናየው  ታላቅ  የፋኖ ትግል የዲያስፓራ ትልቁ ስራ ገንዘብ መስብስብ ነው:: እሱም እየቀዘቀዘ ሄዷል:: ጦርነቱን ያራዝምነው እኛው ነን:: ይህ ደግሞ ትልቁና ዋናው የጠላት ስትራተጂ ነው:: ጦርነቱን ማራዘምና ከአማራ ምድር እንዳይወጣ በማድረግ: ፋኖን በመከፋፈል አዳክመዋለሁ ! እበትነዋለሁ ! የሚል የአቢይ አህመድ ትልቁ  የወቅቱ ስትራተጂ መሆኑን ተረድተናል::: በዚህም ምክንያት በአጠረ ጊዜ  ሊጠናቀቅ የሚችለውን  ትግል  ዲያስፓራ በምቀኝነት: በቅናት: በሌለ  ስልጣን  ላይ በመፋተግ: በተቀጣሪነት: በጠባብ አስተሳስብ: ትግላችንን ወደኋላ  በመጎተትና  እንዲራዘም ብሎም እንዲዳከም በማድረግ ታሪካዊ ወንጀል እየስራ ነው:: ከዚህ መከፋፈል ነፃ ሆነን ፊትለፊት  እየወረረ : እየገደለን: ያለውን የጋራ ጠላታችንን ልናሸንፈው የምንችለው በአንድነት ብቻ ነው::  አሸናፊነት ትብብርና  የጋራ ስትራተጂ ይጠይቃል:: የተግባር ዲያስፓራ እንሁን:: አማራን እንደ  ህዝብ ኢትዮጵያንም እንደ ሀገር  ለማዳን  ዋናው መሳሪያችን  አንድነት ነው:: በውስጣችን ያለውን ልዩነት በመጠቀም  አገራችንን ለማጥፋት: በአካባቢያችን  ያለውን የሀይል አሰላለፍ ስንመለከት ፍፁም ፍፁም  አደገኛ  መሆኑን እንገነዘባለን:: በዲያስፓራ  መጨቃጨቅና መዘላለፍ  እንደ ባህልና እንደ ትልቅ   የጦርነት ስትራተጂ ተደር...

ዐማራን ወክሎ ከወያኔ ጋር ስለሰላምም ሆነ ስለትጥቅ ትግል አልፎም ስለመንግሥት መሥረታ መነጋገር ፈጽሞ አይቻልም

ዐማራን ወክሎ ከወያኔ ጋር ስለሰላምም ሆነ ስለትጥቅ ትግል አልፎም ስለመንግሥት መሥረታ መነጋገር ፈጽሞ አይቻልም፤ ዐማራ የተጨፈጨፈው በሦስት ዓመት ዕድሜ ውስጥ ብቻ አይደለም። በ17 ዓመት የወያኔ የሽፍተነት ዘመን፣ 27 ዓመት የወያኔ የመንግሥትነት ዘመን ወደኋላ ተጨምሮ ነው። ከውያኔ ጋር ሰላምን ወይም ትጥቅ ትግልን እናደርጋለን የሚሉ ሁሉ ውሾች ናቸው። "ውሻ ወደ ትፋቱ ይመለሳል" በምሣሌ 26፤11 እና 2ኛ ጴጥሮስ2፤22 የተጠቀሰውን መጽሐፋዊ ዘገባ በማንበብ ከውያኔ ጋር የመከሩትን የውሾች ባህሪ ለይቶ መረዳት ነው። ምስሉ ጸሃፊውን አይወክልም 1ኛ. የዐማራን ሕዝብ የመደብ ጠላት አድርጎ ወያኔን በደደቢት የመሠረተውና 17 ዓመት በትጥቅ ትግል 27 ዓመት በመንግሥትነት በደምሩ 44 ዓመት ከሰባት ሚሊዮን በላይ ዐማራን ሕዝብ ያለማቋረጥ ያስጨፈጨፈ፣ ርስቱን የነጠቀ በጀምላ የገደለ ያፈናቀለ፣ የትግራይን ሕዝብ ከኢትዮጵያዊ ቀዳሚ ሕዝብነቱና ማንነቱ ያስከዳ ስብሐት ነጋ ፤   2ኛ. ከዐማራ ሕዝብ ይልቅ የሱዳን ሕዝብ ይሻለናል ብሎ በማይካድራ በጭና ዐማራን በከፍተኛ መራር በሆነ ጭካኔ ያስጨፈጨፈው፣ በመጨረሻ ተረጋግቶ መኖር ሲችል ዕቅድና ዓላማ በሌለው ጦርነት አንድ ሚሊዮን የትግራይ ወጣት ያስጨፈጨፈ፣ የትግራይን ሕዝብም ሆነ የዐማራን ሕዝብ አዘቅት ውስጥ የከተተ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ፤   3ኛ. የወያኔ ተሿሚ ሆኖ የዐማራን መሬት ፀገዴና ጠገዴ እያለ እየከፋፈለ ለወያኔ ያስረከበ፣ የግጨውን መሬት ለወያኔ በችሮታ ፈርሞ የሰጠ፤ እነ ዶክተር አባቸው ለማስገደል ቅድመ ሁኔታዎችን ከአመቻቸ በኋላ ወደ አሜሪካ ሀገር ሾልኮ ወጥቶ ከተገደሉ በኋላ ተመልሶ ጥቁር ለብሶ የዓዞ እንባ ሲያነባ ሲመጻደቅ የነበረ የሕወሀትም ሆነ የብልጽግና ቀንደኛና ፊ...

በጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay)

ሻለቃ ዳዊትን በተለያዩ ምክንያቶችና ወቅቶች እንደ እኔ የተቻቸው ፈልጋችሁ አታገኙም። ያ ወቅት ሌላ ፤ ዛሬ ሌላ፤- ያ ዘመን ከ2010 ዓ.ም በፊት ነው። ሰው የነበረውን መስመር አስተካክሎ ባዲስ አካሄድ ወቅቱ በሚጠይቀው ጎዳና ከተራመደ ሌላ ምን ይፈለጋል? ዛሬ ግን ሻለቃው “ኢምፖስተር” በማለት የሚጠሩት ህቡእና ግልጽ ነብሰገዳይ ቡድን አሰማርቶ ነብስን የሚቀጭና የሚሰውር <<የወያኔ የነገድ አስተዳዳር አስቀጣዩ የኦሮሙማው የጋጠወጥ ማፍያዎች መሪ>> አብይ አሕመድ ከነገሠ ወዲህ ግን “ሻለቃው” አብይ አሕመድን እንቅልፍ ካሳጡት አርበኞች አንዱ ሆነው ብቅ ብለዋል። ያንን በማድረጋቸው “ጥበብ ሳሙኤል” የተባለ የአብይ አሕመድ አለቅላቂና ፀረ አማራና የሕግ ሙያ ትምሕርተ አለበት ተብሎ የሚነገርለት (?) ጋዜጠኛ:- አብይ አሕመድን በመደገፍ በሻለቃው ላይ ያለ ዕረፍት ረዢም ጊዜ ሲዘልፋቸው ያስገረመኝ ያህል፤ ሰሞኑን ደግሞ በሻለቃ ዳዊት ወ/ልደጊዮርጊስ ላይ አዳዲስ ዘላፊዎች ብቅ ብለዋል። “ሻለቃ ሆይ! በትግሉ ውስጥ ዛሬ ይኑሩ አይኑሩ አማራውን ለመታደግ ከፍታዎትን አሳይተዋል ፤የበኩልዎን አድርገዋል ለዚህም <<በአክብሮት ባርኔጣየን አነሳለዎታለሁ፤ አንኳን ደስ አለዎት !!!!>> አርበኛ ብቅ ባለ ቁጥር ሱሪውን የሚጎትቱ ብዙ የፖለቲካ ተውሳኮች አሉ። ሻለቃው በዛው ዕደሜአቸው የሚቻላቸውን በማድረጋቸውና ከፍታቸውን በማሳየታቸው ፤ ይህን በማድረጋቸው ዓይናቸው ከቀላ ውስጥ አንዱ ወደ “ጥንት ትፋቱ” የተመለሰው፤ በቅርቡ ከወያኔም ከኦነጎችም እየተወዳደሰ መተፋፋግ የጀመረው የወያኔው አሽከር “ኤርሚያስ ለገሰ” እና ዶ/ር አምሳሉ የተባለ “ከጎንደሬዎች እጅህን አንሳ” እያለ ሲከራከረኝ የነበረው እስከ ቅርብ ጊዜ ወዲህ የአብይ አሕመድ አወዳሽ የነበ...