የአማራ እና የአፋር ሕዝብ በጨካኝ ቡድኖች ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ መልኩ መጠነ ሰፊ ውርጅብኝ እየወረደበትና በግልጽ የዘር ማጥፋት ወንጀል እየተፈጸመበት ይገኛል ። ለሕዝባችን የሚጮህለት ኃይል የለም። የሕዝባችን በደል የሚገደው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ድርጅትም አልተገኘም ። በአጭሩ ለአማራ ሕዝብ ከራሱ ውጪ ማንም እንደማይጮህለት በሚገባ ተረጋግጧል። ስለዚህ በሚቀጥለው ሃሙስ በዋሽንግተን ዲሲ በሚደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ተገኝተው ሰብአዊነትዎን እና ወገናይነትዎን ለአማራና ለአፋር ህዝብ ድምጽ ይሆናሉ ወይስ የተፈጸመባቸውን በደል እያሰቡ ብቻዎትን በቤትዎ ተቀምጠው ያዝናሉ?
ከዚህ መከፋፈል ነፃ ሆነን ፊትለፊት እየወረረ : እየገደለን: ያለውን የጋራ ጠላታችንን ልናሸንፈው የምንችለው ብአንድነት ብቻ ነው:: ሻ/ቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ ሻ/ቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ በምናየው ታላቅ የፋኖ ትግል የዲያስፓራ ትልቁ ስራ ገንዘብ መስብስብ ነው:: እሱም እየቀዘቀዘ ሄዷል:: ጦርነቱን ያራዝምነው እኛው ነን:: ይህ ደግሞ ትልቁና ዋናው የጠላት ስትራተጂ ነው:: ጦርነቱን ማራዘምና ከአማራ ምድር እንዳይወጣ በማድረግ: ፋኖን በመከፋፈል አዳክመዋለሁ ! እበትነዋለሁ ! የሚል የአቢይ አህመድ ትልቁ የወቅቱ ስትራተጂ መሆኑን ተረድተናል::: በዚህም ምክንያት በአጠረ ጊዜ ሊጠናቀቅ የሚችለውን ትግል ዲያስፓራ በምቀኝነት: በቅናት: በሌለ ስልጣን ላይ በመፋተግ: በተቀጣሪነት: በጠባብ አስተሳስብ: ትግላችንን ወደኋላ በመጎተትና እንዲራዘም ብሎም እንዲዳከም በማድረግ ታሪካዊ ወንጀል እየስራ ነው:: ከዚህ መከፋፈል ነፃ ሆነን ፊትለፊት እየወረረ : እየገደለን: ያለውን የጋራ ጠላታችንን ልናሸንፈው የምንችለው በአንድነት ብቻ ነው:: አሸናፊነት ትብብርና የጋራ ስትራተጂ ይጠይቃል:: የተግባር ዲያስፓራ እንሁን:: አማራን እንደ ህዝብ ኢትዮጵያንም እንደ ሀገር ለማዳን ዋናው መሳሪያችን አንድነት ነው:: በውስጣችን ያለውን ልዩነት በመጠቀም አገራችንን ለማጥፋት: በአካባቢያችን ያለውን የሀይል አሰላለፍ ስንመለከት ፍፁም ፍፁም አደገኛ መሆኑን እንገነዘባለን:: በዲያስፓራ መጨቃጨቅና መዘላለፍ እንደ ባህልና እንደ ትልቅ የጦርነት ስትራተጂ ተደር...
Comments