Skip to main content

ምንም ጫጫታ አያስፈልግም ፤ በዐማራ ላይ እየደረሰ ያለው ባርባራዊ በደል የ70 እና የ80 ዓመት ፕሮጀክት ውጤት ነው። በታደለ ጥበቡ Jan 11, 2022 የተጻፈ

በታደለ ጥበቡ  Jan 11, 2022 የተጻፈ ፤ ምንም ጫጫታ አያስፈልግም፣ ዝም ብለን ለብዙ መቶ ዓመት የሚሻግረንን ሥራ በፀጥታ እንሥራ፣ ዛሬ በዐማራ ላይ እየደረሰ ያለው ባርባራዊ በደል የ70 እና የ80 ዓመት ፕሮጀክት ውጤት ነው።

-በጃን ሆይ ዘመን ኢትዮጵያ ውስጥ ይኖር የነበረው  ኦስትሪያዊ ባሮን ሮማን ፕሮቻዝካ (Paron Roman prochazka)  በ1927 ዓ.ም. ቪየና ላይ  "ኢትዮጵያ የባሩድ በርሜል" በሚል ርእስ አውሮፓውያን ኢትዮጵያን እንዴት ሊወሩና ሊይዙ እንደሚባ በሚያትተው መጽሐፉ፣ 

"ምእራባውያን ወገኖቼ ስሙኝ በምስራቅ አፍሪካ በምትገኘው ኢትዮጵያ ውስጥ አንድ ዐማራ የሚባል ነገድ አለ። ይህ ነገድ እኛ ምእራባውያን በአፍሪካ በምናደርገው የመስፋፋት ፖሊሲ ትልቅ እንቅፋት ነው። ዐማራ ከተደራጀ እንኳን ለአፍሪካ ለእኛም ትልቅ ስጋት ስለሆነ በዚህ ህዝብ ላይ እያንዳንዱ ምእራባዊ ሀገር የሚከተለው ፖሊሲ ከዚህ አንፃር መቃኘት አለበት።” (Abyssenya the powder barrel፣ p. 7) በማለት   ይሄን አስፈሪ ነገድ  ነጮች ተባብረው አስቸኳይ እርምጃ እንዲወስዱበት አሳሰበ።

ጣሊያን ይሄን መጽሐፍ እንደ ግባት በመውሰድ በ1928 ዓ.ም. ኢትዮጵያን ስትወር የከፋፍለህ ግዛ (Divided and Rule) ፖሊሲ ተግባራዊ ማድረግ ጀመረች። ትግሬውን በዐማራው ላይ አነሳሳች። ቺኮዝላቫኪያ ተወላጅ የነበሩት አዶልፍ ፓርለሳክ “Habešská Odyssea”በሚለው መጽሐፉ እንደነገረን  ጣልያኖች በትግርኛ ቋንቋ፣ በትግሬ መንደሮች እንዲህ የሚል ወረቀት ይበትኑ ነበር፣

"ለትግራይ ህዝብ!

"በሀገራችሁ ሰላም አስፍነን ስልጣኔና ብልጽግናን እንድናሰፍን እግዚአብሔር ልኮናል። ይሁን እንጂ ዐማራ ሰው በላ ወታደሮቻቸውን አሰልፈውብን ይኼንን የተቀደሰና ከእግዚአብሔር የተሰጠንን ተልዕኮ እንዳንፈጽም እያወኩን ነው። የተከበርክ የትግራይ ህዝብ ሆይ፣ እነዚህን የዐማራ ቀማኛ ሽፍቶች በመንደርህ ሲዘዋወሩ ብታገኝ እህል ውሃ ሳታቀምስ፣ ጥይትህን እየተኮስክ እንደውሻ ከመንደርህ እንድታባርራቸው እናሳስብሀለን።

እነዚህ የዐማራ ሽፍቶች ወደ መንደራችሁ ተጠግተው የሚበላም ሆነ የሚጠጣ ነገር ሊገዙ ቢቀርቡ አብርሯቸው። አዝናችሁም ምንም ነገር፣ ምንም አይነት ርዳታ እንዳታደርጉላቸው አጥብቀን እናሳስባለን። ከማሃላችሁ ይኼን ትዕዛዛችንን ተላልፎ አንድ ሰው እንኳ ለዐማራ የሽፍታ ወታደር አንዲት አንበሻ ሲልግስ ወይም ሲሸጥ ቢገኝ፣ ምህረት የሌለው ቅጣታችን በሁላችሁም ላይ ላይ ይደርሳል።" (የሃበሻ ጀብዱ፣ 214)

በእንዲህ ያለ የፕሮፓጋንዳ ወረቀት የትግራይ ሰዎች ጣሊያንን ለመፋለም ከጎጃም፣ ከጎንደር፣ ከቤተ አምሐራና ከሸዋ የተንቀሳቀሰውን ኢትዮጵያዊ የዐማራ ጦር ሠራዊት በመንደሮቻቸው አካባቢ ሲደርስ ተኩስ ከፍተውበታል፤ ዘርፈውታል፤ ገድለውታል። 

እንደገና ኦሮሞውን በዐማራው ላይ አነሳሳች።

አልቤርቶ ሰባኪ እንደነገረን የጥላቻው ጠቀሜታ ስለታወቀ ኦሮሞዎችን በዐማራዎች ላይ ማነሳሳት አንዱ  የጣሊያን ፕሮፓጋንዳ ማዕከላዊ ነጥብ ነበር። ኦሮሞዎች በጣሊያን እውነተኛ የረጅም ጊዜ ዕቅድ ላይ ጥርጣሬ ስለነበራቸው ጣሊያኖች የኦሮሞዎችን አመኔታ ለማግኘት ዐማሮችን በኦሮሞዎች ፊት ያሰቃይዋቸው ነበረ። ምንም ዓይነት የመቻቻል ምልክት ወይም ለዐማሮች ወገናዊነት ከኦሮሞዎች እንዳያገኙ ይሰሩ ነበረ። (አልቤርቶ ሰባኪ፣ 178)

ጣሊያን ዐማራን በማስጠላት ኢትዮጵያን ለቅኝ ግዛት ለማመቻቸት ያደረገችው ጥረት በአክራሪ ብሔርተኞች ቅቡል ሆነ። የጣሊያንን ፀረ-ዐማራ ፖሊስ ተጋሪ የሆኑ የሀገር ውስጥ በጥላቻ የሰከሩ ብሔርተኞች በዐማራ ጥላቻ ሕግ እና ተቋም ፈጠሩ።

ጣሊያን አገሩን ወርራ እንደያዘችው፣ ሥራዬ ብላ የለፋችው፣ ኢትዮጵያ የሚል ስም ካለም ካርታ ተፍቆ፣ በካርታ ላይ የነበረው ስም የጣሊያን ምሥራቅ አፍሪቃ “Africa Orientale Italiana" እንዲባል ነበር። ትህነግና ኦነግ ደግሞ "ኢትዮጵያዊነትን ዐማራው የጫነብን ዕዳ ነው" በማለት የኢትዮጵያዊነት አስኳል ከውስጣቸው አውጥተው ጣሉት። እንጀራ የዐማራ ስለሆነ አንበላም አሉ። ሸማ ልብስ ያለበሰን ዐማራ ነው በማለት የለበሱትን ሸማ ለማውለቅ ሞከሩ። ሃይማኖት የዐማራ ነው  በማለት በአጉል ማርክሳዊ-ሌኒናዊነት እግዚአብሔር-አልባ ሆኑ። ትዕቢት ወደ ይሉኝታ-ቢስነት ለወጣቸው። የመንፈስ ኃይላቸው ደቀቀ። ወደ ጭራቅነት ተቀየሩ። 

እነዚህ ጭራቆች የነጻነት ግምባር ንቅናቄ አቋቋሙ። ግን ማን ነው ነጻ የሚወጣው? ከማንስ ነው ነጻ የሚወጣው? ብሎ የሚጠይቅ ሰው አይጠፋም። ዶናልድ ሌቪን ለዚህ ጥያቄ መልስ አለው፤ "የማርክሲዝም የእስታሊንን ርዕዮ ዓለም ለማስፋፋት በነጻነት ግንባር ንቅናቄ የተደራጁ ቡድኖች ወክለነዋል የሚሉትን ጎሣቸውን ከማን ነጻ እንደሚያወጡት አንድ ማመካኛ ጨቋኝ መፍጠር ነበረባቸውና እርሱንም ክፉ ብለው በአእምሯቸው በቀረጹት ዐማራ ላይ አገኙት። (ትልቋ ኢትዮጵያ፣ ገጽ -×)

ነገድና ጎሣቸውን ከዐማራ ጨቋኝነት ነፃ እናወጣዋለን ብለው በነፃ አውጭነት ስም የተቧደኑት የመጨረሻ ግባቸው ኢትዮጵያን ዐማራ አድርጎ ሌላው ሁሉ እንደ ኤርትራ  ከ"ዐማራ" ነጻ እንዲወጣ፤ እንዲገነጠል፣ በየአካባቢው ሪፐብሊክ መንግሥት እንዲመሠረት ነው። የኢትዮጵያ ግንባታና ታሪክ ከዐማራ በተወጣጡ ሰዎች ብቻ የተካሄደ ይመስል የኢትዮጵያን ታሪክ ሁሉ ዐማራ ለሚሉት አስረክበው ባዶ እጃቸውን ነጻ ሊወጡ ነው። እናም  ሁሉም ዐማራውን ከሰሱ፣ ዐማራውን የጋራ ጠላት አድርገው ተነሱ፣  ወደ ዐማራው ተኮሱ፣ ዐማራውን አሳደዱ፣ ዐማራውን ገደሉ፣  በአብዮት ስም፣ በተራማጅነት ስም በዐማራ ህዝብ ላይ ሸፈቱ። 

ዛሬም ኦነግና ሕወሓት  በዐማራ ህዝብ ላይ እንደሸፈቱ ናቸው። ኦነግ በኦሮሚያ ዐማራውን ይገድላል፣ ያርዳል፣ ያፈናቅላል፣ የነፍስ አባቱ ሕወሓት ደግሞ ዐማራውን በጅምላ ይጨፈጭፋል፣ አዛውንቶችን ይደፍራል፣ ያፈናቅላል፣ ንብረት ያወድማል።

ለዚህም ነው በዐማራ ላይ የተሰራውን  የ70 እና የ80 ዓመት ፀረ-ዐማራ ፕሮጀክት በሚገባ ተረድተን የመቶ እና የሁለት መቶ ዓመት አሻጋሪ የሆነ  ሰርዶ የነካ ሥራ እንስራ የምንለው። ከማንም ጋር አፍ ተካፍተን፣ ተሰዳድበን አንችለውም። ሥራችን ብቻ በተግባር ይገለጥ። 


ለሀሳብ ለአስተያየትና ጥያቄ ቀጥሎ ያለውን  ሊንክ ይጠቀሙ @Tadeletibebut

Comments

Popular posts from this blog

የጋራ ጠላታችንን ልናሸንፈው የምንችለው ብአንድነት ብቻ ነው:: ሻ/ቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ

ከዚህ መከፋፈል ነፃ ሆነን ፊትለፊት  እየወረረ : እየገደለን: ያለውን የጋራ ጠላታችንን ልናሸንፈው የምንችለው ብአንድነት ብቻ ነው:: ሻ/ቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ ሻ/ቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ በምናየው  ታላቅ  የፋኖ ትግል የዲያስፓራ ትልቁ ስራ ገንዘብ መስብስብ ነው:: እሱም እየቀዘቀዘ ሄዷል:: ጦርነቱን ያራዝምነው እኛው ነን:: ይህ ደግሞ ትልቁና ዋናው የጠላት ስትራተጂ ነው:: ጦርነቱን ማራዘምና ከአማራ ምድር እንዳይወጣ በማድረግ: ፋኖን በመከፋፈል አዳክመዋለሁ ! እበትነዋለሁ ! የሚል የአቢይ አህመድ ትልቁ  የወቅቱ ስትራተጂ መሆኑን ተረድተናል::: በዚህም ምክንያት በአጠረ ጊዜ  ሊጠናቀቅ የሚችለውን  ትግል  ዲያስፓራ በምቀኝነት: በቅናት: በሌለ  ስልጣን  ላይ በመፋተግ: በተቀጣሪነት: በጠባብ አስተሳስብ: ትግላችንን ወደኋላ  በመጎተትና  እንዲራዘም ብሎም እንዲዳከም በማድረግ ታሪካዊ ወንጀል እየስራ ነው:: ከዚህ መከፋፈል ነፃ ሆነን ፊትለፊት  እየወረረ : እየገደለን: ያለውን የጋራ ጠላታችንን ልናሸንፈው የምንችለው በአንድነት ብቻ ነው::  አሸናፊነት ትብብርና  የጋራ ስትራተጂ ይጠይቃል:: የተግባር ዲያስፓራ እንሁን:: አማራን እንደ  ህዝብ ኢትዮጵያንም እንደ ሀገር  ለማዳን  ዋናው መሳሪያችን  አንድነት ነው:: በውስጣችን ያለውን ልዩነት በመጠቀም  አገራችንን ለማጥፋት: በአካባቢያችን  ያለውን የሀይል አሰላለፍ ስንመለከት ፍፁም ፍፁም  አደገኛ  መሆኑን እንገነዘባለን:: በዲያስፓራ  መጨቃጨቅና መዘላለፍ  እንደ ባህልና እንደ ትልቅ   የጦርነት ስትራተጂ ተደር...

ዐማራን ወክሎ ከወያኔ ጋር ስለሰላምም ሆነ ስለትጥቅ ትግል አልፎም ስለመንግሥት መሥረታ መነጋገር ፈጽሞ አይቻልም

ዐማራን ወክሎ ከወያኔ ጋር ስለሰላምም ሆነ ስለትጥቅ ትግል አልፎም ስለመንግሥት መሥረታ መነጋገር ፈጽሞ አይቻልም፤ ዐማራ የተጨፈጨፈው በሦስት ዓመት ዕድሜ ውስጥ ብቻ አይደለም። በ17 ዓመት የወያኔ የሽፍተነት ዘመን፣ 27 ዓመት የወያኔ የመንግሥትነት ዘመን ወደኋላ ተጨምሮ ነው። ከውያኔ ጋር ሰላምን ወይም ትጥቅ ትግልን እናደርጋለን የሚሉ ሁሉ ውሾች ናቸው። "ውሻ ወደ ትፋቱ ይመለሳል" በምሣሌ 26፤11 እና 2ኛ ጴጥሮስ2፤22 የተጠቀሰውን መጽሐፋዊ ዘገባ በማንበብ ከውያኔ ጋር የመከሩትን የውሾች ባህሪ ለይቶ መረዳት ነው። ምስሉ ጸሃፊውን አይወክልም 1ኛ. የዐማራን ሕዝብ የመደብ ጠላት አድርጎ ወያኔን በደደቢት የመሠረተውና 17 ዓመት በትጥቅ ትግል 27 ዓመት በመንግሥትነት በደምሩ 44 ዓመት ከሰባት ሚሊዮን በላይ ዐማራን ሕዝብ ያለማቋረጥ ያስጨፈጨፈ፣ ርስቱን የነጠቀ በጀምላ የገደለ ያፈናቀለ፣ የትግራይን ሕዝብ ከኢትዮጵያዊ ቀዳሚ ሕዝብነቱና ማንነቱ ያስከዳ ስብሐት ነጋ ፤   2ኛ. ከዐማራ ሕዝብ ይልቅ የሱዳን ሕዝብ ይሻለናል ብሎ በማይካድራ በጭና ዐማራን በከፍተኛ መራር በሆነ ጭካኔ ያስጨፈጨፈው፣ በመጨረሻ ተረጋግቶ መኖር ሲችል ዕቅድና ዓላማ በሌለው ጦርነት አንድ ሚሊዮን የትግራይ ወጣት ያስጨፈጨፈ፣ የትግራይን ሕዝብም ሆነ የዐማራን ሕዝብ አዘቅት ውስጥ የከተተ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ፤   3ኛ. የወያኔ ተሿሚ ሆኖ የዐማራን መሬት ፀገዴና ጠገዴ እያለ እየከፋፈለ ለወያኔ ያስረከበ፣ የግጨውን መሬት ለወያኔ በችሮታ ፈርሞ የሰጠ፤ እነ ዶክተር አባቸው ለማስገደል ቅድመ ሁኔታዎችን ከአመቻቸ በኋላ ወደ አሜሪካ ሀገር ሾልኮ ወጥቶ ከተገደሉ በኋላ ተመልሶ ጥቁር ለብሶ የዓዞ እንባ ሲያነባ ሲመጻደቅ የነበረ የሕወሀትም ሆነ የብልጽግና ቀንደኛና ፊ...

በጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay)

ሻለቃ ዳዊትን በተለያዩ ምክንያቶችና ወቅቶች እንደ እኔ የተቻቸው ፈልጋችሁ አታገኙም። ያ ወቅት ሌላ ፤ ዛሬ ሌላ፤- ያ ዘመን ከ2010 ዓ.ም በፊት ነው። ሰው የነበረውን መስመር አስተካክሎ ባዲስ አካሄድ ወቅቱ በሚጠይቀው ጎዳና ከተራመደ ሌላ ምን ይፈለጋል? ዛሬ ግን ሻለቃው “ኢምፖስተር” በማለት የሚጠሩት ህቡእና ግልጽ ነብሰገዳይ ቡድን አሰማርቶ ነብስን የሚቀጭና የሚሰውር <<የወያኔ የነገድ አስተዳዳር አስቀጣዩ የኦሮሙማው የጋጠወጥ ማፍያዎች መሪ>> አብይ አሕመድ ከነገሠ ወዲህ ግን “ሻለቃው” አብይ አሕመድን እንቅልፍ ካሳጡት አርበኞች አንዱ ሆነው ብቅ ብለዋል። ያንን በማድረጋቸው “ጥበብ ሳሙኤል” የተባለ የአብይ አሕመድ አለቅላቂና ፀረ አማራና የሕግ ሙያ ትምሕርተ አለበት ተብሎ የሚነገርለት (?) ጋዜጠኛ:- አብይ አሕመድን በመደገፍ በሻለቃው ላይ ያለ ዕረፍት ረዢም ጊዜ ሲዘልፋቸው ያስገረመኝ ያህል፤ ሰሞኑን ደግሞ በሻለቃ ዳዊት ወ/ልደጊዮርጊስ ላይ አዳዲስ ዘላፊዎች ብቅ ብለዋል። “ሻለቃ ሆይ! በትግሉ ውስጥ ዛሬ ይኑሩ አይኑሩ አማራውን ለመታደግ ከፍታዎትን አሳይተዋል ፤የበኩልዎን አድርገዋል ለዚህም <<በአክብሮት ባርኔጣየን አነሳለዎታለሁ፤ አንኳን ደስ አለዎት !!!!>> አርበኛ ብቅ ባለ ቁጥር ሱሪውን የሚጎትቱ ብዙ የፖለቲካ ተውሳኮች አሉ። ሻለቃው በዛው ዕደሜአቸው የሚቻላቸውን በማድረጋቸውና ከፍታቸውን በማሳየታቸው ፤ ይህን በማድረጋቸው ዓይናቸው ከቀላ ውስጥ አንዱ ወደ “ጥንት ትፋቱ” የተመለሰው፤ በቅርቡ ከወያኔም ከኦነጎችም እየተወዳደሰ መተፋፋግ የጀመረው የወያኔው አሽከር “ኤርሚያስ ለገሰ” እና ዶ/ር አምሳሉ የተባለ “ከጎንደሬዎች እጅህን አንሳ” እያለ ሲከራከረኝ የነበረው እስከ ቅርብ ጊዜ ወዲህ የአብይ አሕመድ አወዳሽ የነበ...