Skip to main content

“እውነትን በማፈን ፍትሃዊ መምሰል አችይልም- ፍትሃዊ አሰራርን በመከተልና በመፈፀም እንጂ”! በወንድወሰን ተክሉ

የአቢይ  መንግስት ፀረ አማራዊ ጋዜጠኞች አክትቪስቶችና ተሟጎቾች ዘመቻ! የአቢይ መራሹ  የብልፅግና  መንግስት  የመከላከያ  ሰራዊቱን  ቅሌታዊ  ሽንፈትን  ተከትሎ  በአስር ሺህ  የሚቆጠሩ  የመከላከያ  አባላትንና  ብሎም ሲቪል  ባለሙያዎችንና የዩንቨርስቲ  ተማሪዎችን  አዘርክርኮ  ከትግራይ  በፈረጠጠ  ማግስት በአማራ  አክትቪስት ጋዜጠኞችና የሰብአዊ  መብት  ተሟጋቾች  ላይ  በመዝመት  ጋሽ ታዲዮስ  ታንቱን  ጨምሮ  ከአስር  በላይ ጋዜጠኞችን  በኢትዮጲያ  አፍሶ  ያሰረ  ሲሆን በተመሳሳይ  ቁጥር  የሚሆኑ  የማህበራዊ ሚዲያ  አንቂዎችን አካውንትን በዘመቻ  መልክ ለማስዘጋት  መቻሉን ማወቅ  ተችሏል::


ይህ የግራፊክ ምስል ጸሃፊውን አይመለከትም

ከጋዜጠኛ  Getachew Shiferaw ሺፈራው  ጀምሮ ጋዜጠኛና አክትቪስት Wondwossen Teklu Wondelove የሰብአዊ መብት ተሟጋች  ቤተልሄም ዳኛቸው Yodith Gideon Dave Dawit Asaminew Tsige Follower  Melkamu Shumye Loul Mekonnen Bahailu_Tessema 

Tina Belay bahailu_tessema Kidist_Garumha እና የመሳሰሉትን  በርካታ አማራዊ አካውንቶች በአጭር  ተመሳስይ  ቀናት  ውስጥ  ማዘጋት  የመቻሉ ጉዳይ  የአቢይ  መራሹን  መንግስት በአማራ  ጉዳይ  ላይ የመዘዘውን አዲስ  ሰይፍ  ያመላክታል:: አማራዊያን ጋዜጠኞች  አክትቪስቶችና የሰብአዊ  መብት ተሟጏቾች  በአቢይ  ጥርስ  ውስጥ  እንዲገቡ ያደረጋቸውና አቢይ ከህዝብ ጆሮ  ለመደበቅ  የፈለገው  ምንድነው?


የአቢይ  መራሹ  የኦህዴድ  ብልፅግና መንግስት  የመከላከያ ሰራዊቱን እያክለፈለፈ  ከትግራይ ያወጣበት ሂደት  ምክንያትና  ብሎም  በክስተቱ  ግንባር  ቀደም  ተጠቂና  የውሳኔው  ገፈት  ቀማሽ  የአማራ  ህዝብና  የመከላከያ  ሰራዊቱ  አባላት  በመሆናቸው  ይህ  ሁለት  የህብረተሰብ  ክፍል የመንግስትን  ምስጢራዊ እርምጃን  እንዳያውቅ  ለማድረግ  መንግስት ይህንንን እውነት ለህዝብ  በማቅረብ  ደረጃ ላይ  ተግተው  በሚሰሩት  ጋዜጠኞች አክትቪስቶችና የሰብአዊ  መብት  ተሟጏቾች  ላይ  በማነጣጠር ልሳናቸውን  ለመዝጋት  እንዲጥር  አድርጎታል::


አቢይ  መራሹ  የኦህዴድ  ብልፅግና  መንግስት  ከአቻ  የብልፅግና አባላት  ማለትም  ከአማራው  ብልፅግና ብአዴን  እና ከመከላከያ  ሰራዊቱ እውቅና እና  ምክክር  ውጪ ከትህነግ  ጋር  በሚስጢር  ሲያደርግ  በነበረው  ምስጢራዊ  ድርድርና  ብሎም  በጦር  ግንባር  በደረሰበት  እሰቃቂ  ሽንፈት  ምክንያት እጅግ  ግብታዊ  ያልተጠና እና  በወታደራዊ  ሳይንስ እቅድና ስልት  ሳይወጣለት  በቅስፈታዊ ድንገት  ከትግራይ  ለቅቆ በመውጣቱ በአስርሺህ  የሚቆጠር  የመከላከያ  ሰራዊት  ህይወት ተቆርጦ  በመቅረትና ተማርኮ አደጋ  ላይ  እንዲወድቅ  ከማስቻሉም  በላይ  በአጠቃላይ  በአማራ  ህዝብ ላይ አዲስ  የጥቃት  አደጋን  የደቀነ  በመሆኑ መንግስት  ጉዳዩን  አዳፍኖ  ለማስቀረት  ሲል  በአማራዊያኑ ጋዜጠኞችና  አክትቪስቶች  ላይ  ለመዝመት   እንደቻለ  መረዳት  ተችሏል::


በዚህ  እርምጃውም  የአቢይ  መራሹ  መንስት የሚጨነቀውና  የሚጠበበው ህዝብና   ሀገር  የሚጎዳ  የስህተት  ውሳኔና  ፖሊሲን  ከማስተላለፍ    ይልቅ   የሰራውን  ጥፋትና  ውድመትን  የምያጋልጡበትን  ሰዎችና  ባለሙያዎች  ላይ  አነጣጥሮ  በማጥቃት  እውነታውን  ማዳፈን  ላይ  መሆኑን   ተግባሮቹ   በትክክል  ይመሰክራሉ:: ለምንድነው  በአስርሺህ  የተቆጠሩ  የመከላከያ  አባላትና ሲቪሊያን ህይወት ሰለባ  በሆነበት ጦርነት   ላይ ትኩረት እና ጥንቃቄን  ከማድረግ ይልቅ  እሱ  በእንዝህላልነት   በግዴለሽነት  በብቃት  ማነስና ወዘተ ምክንያቶች በፈጠረው  ስህተት  የተፈፀመን  ሀገርና  ህዝብ  አፍራሽ  ተግባራትን የሚያጋልጡት  ላይ  ለማነጣጠር  የፈለገው ?


የአቢይ መራሹ  ኦህዴድ/ብልፅግና መንግስት  በአማራ ጋዜጠኞች አክትቪስቶችና  የሰብአዊ መብት  ተሟጏቾች  ላይ  በማነጣጠር  ዘመቻ  ቢከፍተም  እሱ  ሊደብቀው የፈለገውን  እውነት  ግን  ፈፅሞ ሊደብቅ  እንደማይቻለውና  ህዝባችንም ማወቅ  የሚገባውን እውነት  እንዲያውቅ ከማድረግ  አኳያ  ፈፅሞ ሊያቆመን  እንደማይቻለው  ደጋግመን  ልገልፅለት  እንወዳለን::


በመንግስት  በጎፈቃድና  ይሁንታ እውነትን የምንገልፅና  የምንደብቅ ሳይሆን ባለን እማይሻር እማይግሰስና ከቶም እማይሸራርፍ  ተፈጥሮአዊ መብታችንና በግልና በማህበረሰብ ፍላጎታችን  ብቻ ተመርኩዘን  የምንገልፅ  መሆናችንን ማንም  - ወዳጅም ጠላትም- ሊያውቅ  ይገባል:: እውነትን  በማፈን  ሳይሆን ፍትሃዊ መሆን  የሚቻለው  ፍትሃዊ ስራን  በመስራት ብቻ እና ብቻ ነው!


ድል ለሰፊው  የአማራ  ህዝብ!



Comments

Popular posts from this blog

አለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ነኝ የሚለው ቡድን ዓላማ ምንድነው ? በወንድወሰን ተክሉ

ይህ ምስል ጸሃፊውን አይወክልም! «...አማራ ለ450 ዓመታ መንፈሱ የተሰበረ ገበሮ ሕዝብ ነው..» ሀብታሙ ተገኝ (ፕ/ር) « እኔ እስክንድር  የአማራ ሕዝብ ከደረሰበት የህልውና አደጋ እኩል የሚሆን ዓላማ አለው ብዬ አላምንም» አቻምየለህ ታምሩ፤ አለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ነኝ የሚለው ቡድን ዓላማ ምንድነው ? በወንድወሰን ተክሉ እራሱን አለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ነኝ የሚለው ቡድን የዙም ውይይት ፕሮግራም ክፍል ሁለትን የተመለከተ ምልክታ:- ባለፈው  ወር ብቻ ሳይሆን ባለፈው ዓመት ዴሴምበር 2023 ( ዛሬ ጃንዋሪ 1 ቀን 2024 ነን)  እራሱን አለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ ብሎ የሚጠራው ቡድን «ጸረ አማራ ኢትዮጲያዊነት» በሚል አርእስት ስር ሀብታሙ ተገኝ (ፕ/ር) ዋና ተናጋሪ ተጋባዥ የሆነበትን  የዙም ውይይት አካሂዶ የነበረ ሲሆን የዚህ ውይይት ክፍል ሁለት  ባሳለፍነው ወር ዴሴምበር 23ቀን በማዘጋጀት አቻምየለህ ታምሩና ሀብታሙ ተገኝ (ፕ/ር) ተናጋሪ እንግዳ በማድረግ አካሂዷል። በእርግጥ  ከዚህ ከሁለተኛው የውይይት ፕሮግራም በፊት በተክሌ ይሻው በኩል የዙም ሊንክ ተልክሎኝ በሰዓት ጥበት ምክንያት መገኘት ባልችልም ዛሬ ግን በቻናላቸው ላይ የጫኑትን ይህን ክፍል ሁለት ውይይት ከተመለከትኩ በኋላ ይህን ምልክታዬን  አንባቢው ሊረዳ በሚያስችል መልኩ አንድ ሰዓት ከሰላሳ ደቂቃ የፈጀን ውይይት ይዘት በመጭመቅ እንደሚከተለው አቅርቤያለሁ። ይህ ምስል ጸሃፊውን አይወክልም! 1ኛ - ውይይቱን አዘጋጅን ማንነት በተመለከተ፦  አለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ባለፈው መስከረም ወር ላይ  በጌታቸው በየነ ሰብሳቢነት ተመሰረትኩ ብሎ እራሱን ያስተዋወቀ ሲሆን ጌታቸው በየነ ማለት ደግሞ በወቅቱ የ I AM ሰብሳቢ የነበረ እና

The Anti Semitic stand of the OLF : Speech at the Jerusalem Center for Public Affairs in Jerusalem

By Dawit Giorgis The most dangerous crisis in Africa is one unfolding in the Horn of Africa, in Ethiopia. It is a complicated crisis triggered by extremist elements to create an ethnocentric government, which makes one ethnic group superior to all others. The country has been sucked into a quagmire of unending internal wars and terrors that have taken countless  lives, and is characterized by one of the most gruesome crimes in history.  The country has become a failed state, with no  functional central government,  run by a group of ethnic warlords from the Oromia region, where the current PM has been elected.   After the collapse of the brutal regime of the Tigrai People’s Liberation Front (TPLF) by a popular uprising over four years ago, the Oromo-dominated government under Prime Minister Abiy Ahmed has endangered the very foundation of the country. The social fabric of this age-old nation is torn asunder, and the history of the land,  which is rooted in biblical  teachings, is under

"ከአሁን በሆላ ፋኖ ወደ አንድነት መምጣት አለባቸው የሚባለው አካሄድ አይሰራም" :: በወዳጄ/ቤተ አማራ ወሎ

ከአሁን  በሆላ  ፋኖ  ወደ  አንድነት    መምጣት  አለባቸው  የሚባለው  አካሄድ  አይሰራም::  ክህደት   ከተፈፀመ  በሆላ  አንዱ  ቡድን  ከሌላው  ስር  ሆኖ  ይቀጥላል  ማለት  የማይቻል   ነው::  ምክኒያቱም 1ኛ:- 27  ቀን  ቁጪ  ብለው   መክረዋል :: እያንዳንዱ  አደረጃጄት  ሰነድ  ፅፈው  አቅርበዋል::  በቀረበው  ሰነድ  ላይ  ከፍተኛ  ውይይት  ተደርጎበት  የሚወድቀው  ወድቆ  የሚፈለገው  ፀድቋል::ቃለ  መሀላ  ፈፅመው   ወደ  ምርጫ   ለመግባት  ተስማምተዋል:: እጃቸውን  አውጥተው   ከመረጡ  በሆላ    ግን    "ጨዋታ  ፈረሰ  ዳቦ  ተቆረሰ"   የሚል  የህፃን  ልጂ  ጨዋታ  ውስጥ  መግባት   የአማራን  ህዝብም  ሆነ  የፋኖን  ትግል  መናቅ  ነው:: ይህ  አልበቃ  ብሎ   "ምርጫው  ከኛ  እውቅና  ውጪ  ነው  እኛ  አናውቀውም"  የሚል   የውሸት    የህፃን  ልጂ  ፕሮፓጋንዳ   እንዲሰራጪ  አድርገዋል::ከዚህ  በሆላ   ይህ  ቡድን  የታላቁ  እና  የጠቢቡ   የአማራ  ህዝብ  መሪ  ነኝ    ብሎ   አይኑን   በጨው   አጥቦ  ለመምጣት  እንዴትስ  ይደፍራል ????   የድምጽ ቅንብሩ ጸሃፊውን አይወክልም።  2ኛ:- የፋኖ  ወታደራዊ  ጦር  ዋና  አዛዢ   የሆነው  ሻለቃ  ዝናቡ  የራሳቸውን   ድክመት  እና  ሴራ  በአማራ  ህዝብ  ላይ  ለማሸከም   የአማራን  ህዝብ  በጂምላ    ይህ   "ጎጃም  ጠልነት  ነው"   ብሎ  ከወነጄለ  በሆላ   ይቅርታ  ሳይጠየቅበት   በጋራ  ለአንድ  አላማ  እንዴትስ     መስራት  ይቻላል???  የአማራ   ጪምብላቸውን  አውልቀው  እንዴትስ  በመቅፅበት  ወደ  ጎጣቸው   ተወርውረው  ሊገቡ  ቻሉ???  አጄንዳቸው   እንዴትስ