Skip to main content

Posts

Showing posts from May, 2021

ፋሺስቱ ኦህዴዳዊው ስርአት

አሜሪካ - የፋሺስቱ ኦህዴዳዊው አፓርታይዳዊው ስርአት - የከረፋ ወንጀሉን መደበቂያና የህዝብን ድጋፍ መዝረፊያ ፈፅሞ አትሆንም! በወንድወሰን ተክሉ አሜሪካንን ፀረ ኢትዮጲያ የሚያደርግ ክስተትም ሆነ ፀረ አሜሪካዊ ኃይል በዛሬይቱ ኢትዮጲያ አለ? በኢትዮጲያነት ስሜት የተሰራው የእስከዛሬው ወንጀል ስቃይና መከራ ከእንግዲህ ላይቀጥል መበጣጠስ ያለበት አሁን ዛሬ ነው:: ፋሺስቱ የአቢይ መራሹ አፓርታይዳዊ ስርአት ከጀሌዎቹ ኢዜማ ጋር በመሆን አሜሪካ ኢትዮጲያን እንደሊቢያ ልታደርግ የተነሳች ቀንደኛ ጭራቅ ናት በማለት የህዝብን attention እና ድጋፍ mobilize ለማድረግ ሲንቀሳቀሱ ታይቷል:: መንጋውም - በተለይ በተለይ ምንም መማር ያልቻለው በስሜት ጋላቢ መንጋ ይህንን መንግስት መር ፕሮፖጋንዳን በማስተጋባት ፈጥኖ ሲሰለፍ ታይቷል:: የግራፊክ ምስሉ ጸሃፊውን አይወክልም! በእርግጥ አሜሪካ ኢትዮጲያን የመበትን አላማ እቅድና ፍላጎት አላትን ? ካላትስ ለምን እና እንዴት  ብሎ ከመጠየቅ የተወረወረለትን አጥንት ለቀም አድርጎ እንደሚሮጥ ውሻ እነዚህ መሰሪዎች የወረወሩለትን የሴራና የፈጠራ ወሬን ብድግ አድርገው ሲያራግቡ ይታያል:: ተመልከቱ ይህ ለብልፅግና መንግስት እነ XYZ የፖለቲካ ኃይሎች ይመቱ በሽብርተኝነት ይፈረጁ ሚዲያዎች ይዘጉ እያለ ጥናት በማቅረብ የኢትዮጲያን ሀገረ ዴሞክራሲን ግንባታን በማደናቀፍ ቀንደኛ ጨፍጫፊ ፋሺስት ስርአትን እየፈጠረ ያለው የኢዜማው ስብስብ ሀገር ወዳድ መስሎ እና እራሱን ለሀገር ተቆርቋሪ አድርጎ አሜሪካንን እየጠራ ሲፎክር አይታችሁ እንኳን መረዳት አትችሉምን? የኢትዮጲያን ህልውና አደጋ ላይ የጣለው የአሜሪካ ተፅእኖ ሳይሆን የአቢይና ኢዜማ ፋሺስታዊ አምባገነንነት ሆኖ ሳለ ዛሬ እነዚሁ ስብስቦች ሀገር በአሜሪካ ጣልቃ ገብነት ልትፈርስ ነው

“አዲሱ የትግራይ ትውልድ የትህነግን ትርክት ሳያራግፍ ከአማራ ጋር ሰላማዊ የጉርብትና አኗኗር መፍጠር አይቻልም”

ለርእዮቱ ጋዜጠኛ ቴውድሮስ ጸጋዬ የተሰጠ መልስ: - በወንድወሰን ተክሉ  👉ወልቃይት ጠገዴ ሁመራ ዳንሻና ራያን ከአማራ አስተዳደር ስር አይደለም የተደመሰሰችው ትህነግም ሆነች TDF ይቅርና ተስፋ ያደረጋችኋት አሜሪካም አታስመልስላችሁም-ለሰላማዊ ጉርብትናችን መጀመሪያ የትህነግን ትርክትን መቅበርና ወረራዋን ማውገዝ የአማራ ልዩ ኃይል ሚሊሺያና ፋኖ በምእራባዊው የትግራይ ግዛት (ወልቃይት ጠገዴ ሁመራ ዳንሻ ) በዘረፋ ላይ ተሰማርተዋል የሚለው የቴድርስ ጸጋዬ የእለተ ቅዳሜ ውንጀላ ለዚህ የአጸፋ ምላሽ ጽሁፌ መሰረት እንደሆነኝ በቅድሚያ መግለጹ ተገቢ ይመስልኛል፡፡ ፎቶውና ሎጎው ጸሃፊውን አይወክልም! በብርቱ ተሟጋችነቱ በኢትዮጲያ አንድነት አቀንቃኝነቱ እማደንቀውና እማከብረው የርእዮቱ ሚዲያ አዘጋጅ ጋዜጠኛ ቴድሮስ ጸጋዬ በቅዳሜ እለት ፕሮግራሙ ከጋበዘው ክፍሉ ሁሴን ጋር በመሆን መጀመሪያ በአማራ ልዩ ኃይል ሚሊሻና ፋኖ ላይ ቀስና ለስለስ አድርጎ የጀመረውን የነቀፋና ውንጀላን በማጠናከርና ብሎም በማክረር አጠቃላይ ዘለፋዎቹንና ውንጀላዎቹን በአማራ ህዝብ ላይ በማድረግ ከክፍሉ ሁሴን ጋር እየተቀባበሉ አማራንና የአማራ ብሄርተኝነትን ጥንብ እርኩሱን እያወጡ ሲያወግዙ እጅግ እየገረመኝና እየደነቀኝ አደመጥኩ፡፡ የአድናቆቴና አግራሞቴም መፍለቂያ መንስኤም ይህ አንድን ህዝብ በጅምላ ብድግ አድርጎ የመዝለፍ የመወንጀልና ብሎም የመንቀፉ ሁኔታን በተለይ በተለይ ከቴድሮስ ጸጋዬ አንደበት እየተደመጠ ያለ የመሆኑ ጉዳይ ሲሆን ጋዜጠኛ ቴድሮስ ጸጋዬ በኢትዮጲያ ሀገራዊ አንድነትና ህልውና ፣ በአዲስ አበባ የህልውና ትግል፣በአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ላይና ብሎም በኦህዴድ መራሹ የብልጽግና መንግስት ላይ ያለውን የማይናወጥ ጽኑ አቋማዊ መረዳት ይህንን የእለተ ቅዳሜውን ውግዘተ -አማራን በእኔ

በመንግስት የተደገፈ ሽብርተኝነት

 ኦነግ (OLF) የተባለው ነፍሰ ገዳይ ቡድን ፤ በአብይ አህመድ የስውር መዋቅር ውስጥ ፤ በዘመናዊ መሳሪያ ተደራጅተውና ተጠናክረው ያሉ  የኦሮሙማ ተስፋፊ አሸባሪ ቡድን ናቸው። በመንግስት መኪና ተጭነው ፤ ሙሉ የውታደራዊ ሎጀስቲክ ቀርቦላቸው ፤ በነጻነት በሃገሪቱ ክፍል እየተዘዋወሩ  የንፁሀን አማራ ደም የሚያፈሱ ፤ የተረኛው የአብይ አህመድ ነፍሰ ገዳይ ውታደሮች ናቸው።  በአማራ ህዝብ ላይ የሚያደርሰውን ዘግኛኝ ጭፍጨፋና የዘር ማጥፋት ወንጀል ለአለም ህዝብ ለማሳወቅ ሁላችንም በምንችለው መንገድ መስራት ይኖርብናል ። ከዚህ በላይ የሚታየው ቪዲዬ በአማራ ህዝብ ላይ የተፈጸመውን የጅምላ ግድያና የንብረት ውድመት የሚያሳይ ነው ። የቪዲዬ ማጫወቻ ምልክት ይጫኑትና  ይመልከቱት ፤ ከዚያም ለወዳጅ ዘመድ ሼር ያድርጉት ፤ እናመሰግናለን!