Skip to main content

Posts

Showing posts from July, 2021

ኢትዮጵያን ለማፈራረስ የተጸነሰው ሴራ ይፋ ሆነ ፤ ኢትዮጵያን ከመፈራረስ ለመታደግ በአንድነት መቆም ነው— በዶ/ር አክሎግ ቢራራ

እኔ እስከማውቀው ድረስ፤ የምእራብ አገሮች ለጥቁር አፍሪካ ሕዝቦች ሰላም፤ እርጋታ፤ ክብር፤ ነጻነት፤ ፍትሃዊና ዘላቂ ልማት ቆመው አያውቁም። በተለይ፤ ለመላው የጥቁር ሕዝብ ክብርና ነጻነት ተምሳሌ የሆነችውን የኢትዮጵያን ግዛታዊ አንድነት፤ ሉዐላዊነት፤ የስብጥር ሕዝቧን አብሮነት፤ ሰላም፤ እርጋታ፤ ፍትሃዊ፤ ዘላቂ ብልጽግና ደግፈው አያውቁም። የኢትዮጵያ ጠንካራና አገር ወዳድ መንግሥት ለነሱ ብሄራዊ ጥቅም ስጋት ፈጣሪ ነው። ይኼን ሃቅ በአጼ ኃይለ ሥላሴና በደርግ መንግሥት ወቅትም አይተናል።  ህወሓት/ትህነግ ጆ ባይደን በተመረጡበት ማግስት ክህደት፤ እልቂት ከፈጸመበትና ጦርነት ከጀመረበት አንድ ሳምንት በኋላ ለዚህ አጥፊ፤ ከሃዲና የውጭ ኃይሎች አገልጋይና አሽከር የሆነ ቡድን ግዙፍ ድጋፍ ይሰጡት የነበሩት የምእራብ “ዲሞክራሲ” ነን የሚሉ ባለሥልጥናት ሴራቸውን በምስጢር ቀየሱ።  ኢላማቸው ሁለት አስኳል ጉዳዮች ነበሩ፤ አንድ የጠቅላይ ሚንስትር ዶር ዐብይ አሕመድን መንግሥት መገልበጥና ባለሥልጣናትን ልክ እንደ ሰርቦች ለፍርድ ማቅረብ፤ ሁለት፤ ኢትዮጵያ ልክ እንደ ዩጎስላቭያና እንደ ሶማልያ እንድትበታተን ማድረግ።  እኛ አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን በተደጋጋሚ ለምእራብ አገሮች ባለሥልጣናት፤ በተለይ ለአሜሪካ ምክር ቤት አባላት በተደጋጋሚ እባካችሁ ሚዛናዊ አቋም ያዙ፤ በመሬት ላይ ያለውን ሃቅ አንጸባርቁ፤ የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል የትግራይ ሕዝብ ጠላት አይደለም፤ የብሄር ማጥፋት ዘመቻ አያካሂድም፤ የኢትዮጵያ መንግሥት 70 በመቶ የሚሆነውን ሰብአዊ እርዳታ እየሰጠ ነው ወዘተ እያልን ብንጮህም ሰሚ አላገኘነም ነበር። ብዙዎቻችን ግራ ተጋብተን ነበር ለማለት እችላለሁ። ለምን ጀሩቸውን አይከፍቱም፤ አይናቸውን አይገልጡም? እንል ነበር፡ ከጀርባ በረቀቀ ምስጢር የሚካሄደውን ሴራ

JOURNALISM IS NOT CRIME

የአማራ ሚዲያ ማዕከል ጋዜጠኛ  ለድምጽ አልባው ወገናችን ፤ ድምፅ በመሆን የሚታወቀው ጋዜጠኛ አባይ ዘውዱ በነውረኛው የአማራ ብልጽግና ፓርቲ እና በአብይ አህመድ  አፋኝ ቡድኖች አሳፍነው ወዳልታወቀ ቦታ ወስደውታል።  Abay Zewdu, AMC reporter & Journalist Free Abay Zewdu   ድምጽን ለማፈን መሞከር ከቶውንም አይቻልምና ፤ በአስቸኳይ ጋዜጤኛ አባይ ዘውዱን ፍቱት!  Free AMC Journalist

“እውነትን በማፈን ፍትሃዊ መምሰል አችይልም- ፍትሃዊ አሰራርን በመከተልና በመፈፀም እንጂ”! በወንድወሰን ተክሉ

የአቢይ  መንግስት ፀረ አማራዊ ጋዜጠኞች አክትቪስቶችና ተሟጎቾች ዘመቻ! የአቢይ መራሹ  የብልፅግና  መንግስት  የመከላከያ  ሰራዊቱን  ቅሌታዊ  ሽንፈትን  ተከትሎ  በአስር ሺህ  የሚቆጠሩ  የመከላከያ  አባላትንና  ብሎም ሲቪል  ባለሙያዎችንና የዩንቨርስቲ  ተማሪዎችን  አዘርክርኮ  ከትግራይ  በፈረጠጠ  ማግስት በአማራ  አክትቪስት ጋዜጠኞችና የሰብአዊ  መብት  ተሟጋቾች  ላይ  በመዝመት  ጋሽ ታዲዮስ  ታንቱን  ጨምሮ  ከአስር  በላይ ጋዜጠኞችን  በኢትዮጲያ  አፍሶ  ያሰረ  ሲሆን በተመሳሳይ  ቁጥር  የሚሆኑ  የማህበራዊ ሚዲያ  አንቂዎችን አካውንትን በዘመቻ  መልክ ለማስዘጋት  መቻሉን ማወቅ  ተችሏል:: ይህ የግራፊክ ምስል ጸሃፊውን አይመለከትም ከጋዜጠኛ  Getachew Shiferaw ሺፈራው  ጀምሮ ጋዜጠኛና አክትቪስት Wondwossen Teklu Wondelove የሰብአዊ መብት ተሟጋች  ቤተልሄም ዳኛቸው Yodith Gideon Dave Dawit Asaminew Tsige Follower  Melkamu Shumye Loul Mekonnen Bahailu_Tessema  Tina Belay bahailu_tessema Kidist_Garumha እና የመሳሰሉትን  በርካታ አማራዊ አካውንቶች በአጭር  ተመሳስይ  ቀናት  ውስጥ  ማዘጋት  የመቻሉ ጉዳይ  የአቢይ  መራሹን  መንግስት በአማራ  ጉዳይ  ላይ የመዘዘውን አዲስ  ሰይፍ  ያመላክታል:: አማራዊያን ጋዜጠኞች  አክትቪስቶችና የሰብአዊ  መብት ተሟጏቾች  በአቢይ  ጥርስ  ውስጥ  እንዲገቡ ያደረጋቸውና አቢይ ከህዝብ ጆሮ  ለመደበቅ  የፈለገው  ምንድነው? የአቢይ  መራሹ  የኦህዴድ  ብልፅግና መንግስት  የመከላከያ ሰራዊቱን እያክለፈለፈ  ከትግራይ ያወጣበት ሂደት  ምክንያትና  ብሎም  በክስተቱ  ግንባር  ቀደም  ተጠቂና  የውሳኔው